1Taigi būkite Dievo sekėjai, kaip mylimi vaikai,
1እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥
2ir gyvenkite mylėdami, kaip ir Kristus pamilo mus ir atidavė už mus save kaip atnašą ir kvapią auką Dievui.
2ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።
3Todėl ištvirkavimas, visoks netyrumas ar godumas tenebūna net minimi pas jus, kaip pridera šventiesiems;
3ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኵሰት ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ፤
4taip pat nešvankumas, kvaila šneka ar juokų krėtimas jums netinka, verčiau tebūna dėkojimas.
4የሚያሳፍር ነገርም የስንፍና ንግግርም ወይም ዋዛ የማይገቡ ናቸውና አይሁኑ፥ ይልቁን ምስጋና እንጂ።
5Nes jūs žinote, kad joks ištvirkėlis, netyras ar gobšas, kuris yra stabmeldys, nepaveldės Kristaus ir Dievo karalystės.
5ይህን እወቁ፤ አመንዝራም ቢሆን ወይም ርኵስ ወይም የሚመኝ እርሱም ጣዖትን የሚያመልክ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መንግሥት ርስት የለውም።
6Tegul niekas neapgauna jūsų tuščiais plepalais; už tokius dalykus Dievo rūstybė ištinka neklusnumo vaikus.
6ከዚህ የተነሣ በማይታዘዙት ልጆች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣልና ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ።
7Todėl nebūkite jų bendrai!
7እንግዲህ ከእነርሱ ጋር ተካፋዮች አትሁኑ፤
8Juk kadaise buvote tamsa, o dabar esate šviesa Viešpatyje. Elkitės kaip šviesos vaikai,
8ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፤
9nes Dvasios vaisius reiškiasi visokeriopu gerumu, teisumu ir tiesa,
9የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤
10ištirdami, kas patinka Viešpačiui.
11ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፥ ይልቁን ግለጡት እንጂ፥
11Ir neprisidėkite prie nevaisingų tamsos darbų, o verčiau atskleiskite juos.
12እነርሱ በስውር ስለሚያደርጉት መናገር እንኳ ነውር ነውና፤
12Nes ką jie slapčia daro, gėda net sakyti.
13ሁሉ ግን በብርሃን ሲገለጥ ይታያል፤ የሚታየው ሁሉ ብርሃን ነውና።
13Bet viskas, kas atskleidžiama, tampa šviesos apšviesta, o kas tik apšviesta, yra šviesa.
14ስለዚህ። አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል።
14Todėl sakoma: “Pabusk, kuris miegi, kelkis iš numirusių, ir apšvies tave Kristus”.
15እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፤
15Todėl rūpestingai žiūrėkite, kaip elgiatės: kad nebūtumėte kaip kvailiai, bet kaip išmintingi,
16ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ።
16branginantys laiką, nes dienos yra piktos.
17ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደ ሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ።
17Nebūkite tad neprotingi, bet supraskite, kokia yra Viešpaties valia.
18መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና፤
18Ir nepasigerkite vynu, kuriame pasileidimas, bet būkite pilni Dvasios,
19በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤
19kalbėdami vieni kitiems psalmėmis, himnais bei dvasinėmis giesmėmis, giedodami ir šlovindami savo širdyse Viešpatį,
20ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።
20visada ir už viską dėkodami Dievui Tėvui mūsų Viešpaties Jėzaus Kristaus vardu,
21ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ።
21paklusdami vieni kitiems Dievo baimėje.
22ሚስቶች ሆይ፥ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤
22Jūs, žmonos, būkite klusnios savo vyrams lyg Viešpačiui,
23ክርስቶስ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ እርሱም አካሉን የሚያድን እንደ ሆነ ባል የሚስት ራስ ነውና።
23nes vyras yra žmonos galva, kaip ir Kristus yra galva bažnyčios,Jis kūno gelbėtojas.
24ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ።
24Todėl kaip bažnyčia paklūsta Kristui, taip ir žmonos visame kame teklauso savo vyrų.
25ባሎች ሆይ፥ ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤
25Jūs, vyrai, mylėkite savo žmonas, kaip ir Kristus pamilo bažnyčią ir atidavė už ją save,
27እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።
26kad ją pašventintų, apvalydamas vandens nuplovimu ir žodžiu,
28እንዲሁም ባሎች ደግሞ እንደ ገዛ ሥጋቸው አድርገው የገዛ ሚስቶቻቸውን ሊወዱአቸው ይገባቸዋል። የገዛ ሚስቱን የሚወድ ራሱን ይወዳል፤
27kad pristatytų sau šlovingą bažnyčią, neturinčią dėmės nei raukšlės, nei nieko tokio, bet šventą ir nesuteptą.
29ማንም የገዛ ሥጋውን የሚጠላ ከቶ የለምና፥ ነገር ግን የአካሉ ብልቶች ስለሆንን፥ ክርስቶስ ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን እንዳደረገላት፥ ይመግበዋል ይከባከበውማል።
28Taip ir vyrai turi mylėti savo žmonas kaip savo kūnus. Kas myli savo žmoną, myli save patį.
31ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።
29Juk niekas niekada nėra nekentęs savo kūno, bet jį maitina ir globoja kaip ir Kristus bažnyčią.
32ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው፥ እኔ ግን ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እላለሁ።
30Mes gi esame Jo kūno nariai, iš Jo kūno ir kaulų.
33ሆኖም ከእናንተ ደግሞ እያንዳንዱ የገዛ ሚስቱን እንዲህ እንደ ራሱ አድርጎ ይውደዳት፥ ሚስቱም ባልዋን ትፍራ።
31“Todėl žmogus paliks tėvą bei motiną ir susijungs su savo žmona, ir du taps vienu kūnu”.
32Tai didelė paslaptis,aš tai sakau, žvelgdamas į Kristų ir bažnyčią.
33Taigi kiekvienas iš jūsų tegul myli savo žmoną taip, kaip save patį, o žmona tegerbia savo vyrą.