1Trečią dieną Galilėjos Kanoje buvo vestuvės. Jose dalyvavo Jėzaus motina.
1በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ነበረ፥ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፤
2Į vestuves buvo pakviestas ir Jėzus, ir Jo mokiniai.
2ኢየሱስም ደግሞ ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ።
3Pritrūkus vyno, Jėzaus motina Jam sako: “Jie nebeturi vyno”.
3የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት። የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው።
4Jėzus jai atsakė: “O kas man ir tau, moterie? Dar neatėjo mano valanda”.
4ኢየሱስም። አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት።
5Jo motina tarė tarnams: “Darykite, ką tik Jis jums lieps”.
5እናቱም ለአገልጋዮቹ። የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው።
6Ten buvo šeši akmeniniai indai žydų apsiplovimams, kiekvienas dviejų trijų saikų talpos.
6አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር።
7Jėzus jiems liepė: “Pripilkite indus vandens”. Jie pripylė sklidinus.
7ኢየሱስም። ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው።
8Tada Jis sakė: “Dabar semkite ir neškite stalo prižiūrėtojui”. Tie nunešė.
8አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው፤ ሰጡትም።
9Paragavęs paversto vynu vandens ir nežinodamas, iš kur tai (bet tarnai, kurie sėmė vandenį, žinojo), prižiūrėtojas pasišaukė jaunikį
9አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ።
10ir tarė jam: “Kiekvienas žmogus pirmiau stato geresnio vyno, o kai svečiai įgeria, tuomet prastesnio. O tu laikei gerąjį vyną iki šiol”.
10ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል አለው።
11Tokią stebuklų pradžią Jėzus padarė Galilėjos Kanoje. Taip Jis parodė savo šlovę, ir mokiniai įtikėjo Jį.
11ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።
12Paskui Jis su savo motina, broliais ir mokiniais nukeliavo į Kafarnaumą. Ten jie pasiliko kelias dienas.
12ከዚህ በኋላ ከእናቱና ከወንድሞቹ ከደቀ መዛሙርቱም ጋር ወደ ቅፍርናሆም ወረደ፥ በዚያም ጥቂት ቀን ኖሩ።
13Artėjant žydų Paschai, Jėzus nukeliavo į Jeruzalę.
13የአይሁድ ፋሲካም ቀርቦ ነበር፥ ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ።
14Šventykloje Jis rado prekiaujančių jaučiais, avimis, karveliais ir prisėdusių pinigų keitėjų.
14በመቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤
15Susukęs iš virvučių rimbą, Jis išvijo juos visus iš šventyklos, išvarė avis ir jaučius, išbarstė keitėjų pinigus ir išvartė stalus.
15የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥
16Karvelių pardavėjams Jis sakė: “Pasiimkite visa tai iš čia ir iš mano Tėvo namų nedarykite prekybos namų!”
16ርግብ ሻጪዎችንም። ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።
17Ir Jo mokiniai prisiminė, kad yra parašyta: “Uolumas dėl Tavo namų sugrauš mane”.
17ደቀ መዛሙርቱም። የቤትህ ቅናት ይበላኛል ተብሎ እንደ ተጻፈ አሰቡ።
18Tada žydai kreipėsi į Jį, sakydami: “Kokį ženklą mums parodysi, jog turi teisę taip daryti?”
18ስለዚህ አይሁድ መልሰው። ይህን ስለምታደርግ ምን ምልክት ታሳየናለህ? አሉት።
19Jėzus atsakė: “Sugriaukite šitą šventyklą, ir per tris dienas Aš ją atstatysiu!”
19ኢየሱስም መልሶ። ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው።
20Tada žydai sakė: “Keturiasdešimt šešerius metus šventyklą statė, o Tu atstatysi ją per tris dienas?!”
20ስለዚህ አይሁድ። ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥ አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን? አሉት።
21Bet Jis kalbėjo apie savo kūno šventyklą.
21እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር።
22Todėl, Jam prisikėlus iš numirusių, Jo mokiniai prisiminė Jį apie tai kalbėjus ir jie įtikėjo Raštu ir Jėzaus pasakytu žodžiu.
22ስለዚህ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ይህን እንደ ተናገረ አሰቡና መጽሐፍንና ኢየሱስ የተናገረውን ቃል አመኑ።
23Per Paschos šventę, Jam būnant Jeruzalėje, daugelis įtikėjo Jo vardą, matydami Jo daromus ženklus.
23በፋሲካ በዓልም በኢየሩሳሌም ሳለ፥ ያደረገውን ምልክት ባዩ ጊዜ ብዙ ሰዎች በስሙ አመኑ፤
24Bet Jėzus, gerai visus pažindamas, jais nepasitikėjo.
24ነገር ግን ኢየሱስ ሰዎችን ሁሉ ያውቅ ነበር፤ ስለ ሰውም ማንም ሊመሰክር አያስፈልገውም ነበርና አይተማመናቸውም ነበር፤ ራሱ በሰው ያለውን ያውቅ ነበርና።
25Jam nereikėdavo, kad kas paliudytų apie žmogų, nes Jis pats žinojo, kas yra žmoguje.