Lithuanian

Amharic: New Testament

John

3

1Buvo vienas fariziejus, vardu Nikodemas, žydų vyresnysis.
1ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ።
2Jis atėjo naktį pas Jėzų ir kreipėsi į Jį: “Rabi, mes žinome, kad esi mokytojas, atėjęs nuo Dievo, nes niekas negalėtų daryti tokių ženklų, kokius Tu darai, jeigu Dievas nebūtų su juo”.
2መምህር ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን አለው።
3Jėzus jam atsakė: “Iš tiesų, iš tiesų sakau tau: jei kas negims iš naujo, negalės regėti Dievo karalystės”.
3ኢየሱስም መልሶ። እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው።
4Nikodemas paklausė: “Bet kaip gali gimti žmogus, būdamas senas? Argi jis gali antrą kartą įeiti į savo motinos įsčias ir gimti?”
4ኒቆዲሞስም። ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው።
5Jėzus atsakė: “Iš tiesų, iš tiesų sakau tau: jei kas negims iš vandens ir Dvasios, negalės įeiti į Dievo karalystę.
5ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል። እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም።
6Kas gimė iš kūno, yra kūnas, o kas gimė iš Dvasios, yra dvasia.
6ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው።
7Nesistebėk, jog pasakiau tau: jums būtina gimti iš naujo.
7ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋችኋል ስላልሁህ አታድንቅ።
8Vėjas pučia, kur nori; jo ošimą girdi, bet nežinai, iš kur ateina ir kurlink nueina. Taip yra su kiekvienu, kuris gimė iš Dvasios”.
8ነፋስ ወደሚወደው ይነፍሳል፥ ድምፁንም ትሰማለህ፥ ነገር ግን ከወዴት እንደ መጣ ወዴትም እንዲሄድ አታውቅም፤ ከመንፈስ የተወለደ ሁሉ እንዲሁ ነው።
9Nikodemas atsiliepė: “Kaip tai gali būti?”
9ኒቆዲሞስ መልሶ። ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? አለው።
10Jėzus jam atsakė: “Tu esi Izraelio mokytojas ir šito nesupranti?
10ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው። አንተ የእስራኤል መምህር ስትሆን ይህን አታውቅምን?
11Iš tiesų, iš tiesų sakau tau: mes kalbame, ką žinome, ir liudijame, ką matėme, o jūs nepriimate mūsų liudijimo.
11እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ምስክራችንንም አትቀበሉትም።
12Jei netikite man kalbant apie žemiškuosius dalykus, tai kaipgi tikėsite, jei kalbėsiu jums apie dangiškuosius?
12ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ፥ ስለ ሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ?
13Niekas nėra pakilęs į dangų, kaip tik Tas, kuris nužengė iš dangaus,­Žmogaus Sūnus, esantis danguje.
13ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው።
14Kaip Mozė dykumoje iškėlė gyvatę, taip turi būti iškeltas Žmogaus Sūnus,
14ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል።
15kad kiekvienas, kuris Jį tiki, nepražūtų, bet turėtų amžinąjį gyvenimą”.
16በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።
16Nes Dievas taip pamilo pasaulį, jog atidavė savo viengimį Sūnų, kad kiekvienas, kuris Jį tiki, nepražūtų, bet turėtų amžinąjį gyvenimą.
17ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ፥ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና።
17Dievas gi nesiuntė savo Sūnaus į pasaulį, kad Jis pasaulį pasmerktų, bet kad pasaulis per Jį būtų išgelbėtas.
18በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል።
18Kas Jį tiki, tas neteisiamas, o kas netiki, jau yra pasmerktas už tai, kad netiki viengimio Dievo Sūnaus vardo.
19ብርሃንም ወደ ዓለም ስለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነው።
19O teismo nuosprendis yra toks: šviesa atėjo į pasaulį, bet žmonės labiau pamilo tamsą nei šviesą, nes jų darbai buvo pikti.
20ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም፤
20Kiekvienas, kuris daro bloga, neapkenčia šviesos ir neina į šviesą, kad jo darbai nebūtų atskleisti.
21እውነትን የሚያደርግ ግን ሥራው በእግዚአብሔር ተደርጎ እንደ ሆነ ይገለጥ ዘንድ ወደ ብርሃን ይመጣል።
21O kas vykdo tiesą, tas eina į šviesą, kad pasirodytų, jog jo darbai atlikti Dieve.
22ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ይሁዳ አገር መጣ፥ በዚያም ከእነርሱ ጋር ተቀምጦ ያጠምቅ ነበር።
22Paskui Jėzus su savo mokiniais atėjo į Judėjos kraštą ir, ten su jais būdamas, krikštijo.
23ዮሐንስም ደግሞ በሳሌም አቅራቢያ በሄኖን በዚያ ብዙ ውኃ ነበርና ያጠምቅ ነበር፥
23Taip pat ir Jonas krikštijo Enone, netoli Salimo, nes ten buvo daug vandens ir žmonės ten ateidavo ir buvo krikštijami.
24እየመጡም ይጠመቁ ነበር ዮሐንስ ገና ወደ ወኅኒ አልተጨመረም ነበርና።
24Tada Jonas dar nebuvo įmestas į kalėjimą.
25ስለዚህም በዮሐንስ ደቀ መዛሙርትና በአይሁድ መካከል ስለ ማንጻት ክርክር ሆነ።
25Tarp Jono mokinių ir vieno žydo kilo ginčas dėl apsivalymo.
26ወደ ዮሐንስም መጥተው። መምህር ሆይ፥ በዮርዳኖስ ማዶ ከአንተ ጋር የነበረው አንተም የመሰከርህለት፥ እነሆ፥ እርሱ ያጠምቃል ሁሉም ወደ እርሱ ይመጣሉ አሉት።
26Tad jie atėjo pas Joną ir pranešė: “Rabi, Tas kuris buvo su tavimi anapus Jordano, apie kurį tu paliudijai,­štai Jis krikštija, ir visi eina pas Jį”.
27ዮሐንስ መለሰ፥ እንዲህ ሲል። ከሰማይ ካልተሰጠው ሰው እንዳች ሊቀበል አይችልም።
27Jonas atsakė: “Žmogus nieko negali pasiimti, jeigu jam neduota iš dangaus.
28እናንተ። እኔ ክርስቶስ አይደለሁም፥ ነገር ግን። ከእርሱ በፊት ተልኬአለሁ እንዳልሁ ራሳችሁ ትመሰክሩልኛላችሁ።
28Jūs patys galite man paliudyti, jog sakiau: aš ne Kristus! Aš siųstas būti tik Jo pirmtaku.
29ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው፤ ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል። እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ።
29Kas turi sužadėtinę, tas sužadėtinis, o sužadėtinio bičiulis, kuris šalia stovi ir jį girdi, džiaugte džiaugiasi jaunikio balsu. Todėl šiam mano džiaugsmui jau nieko netrūksta.
30እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል።
30Jis turi augti, o aš­mažėti”.
31ከላይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው፤ ከምድር የሚሆነው የምድር ነው የምድሩንም ይናገራል። ከሰማይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው።
31Kas iš aukštybių ateina, Tas už visus viršesnis, o kas iš žemės,­ žemiškas yra ir žemiškai kalba. Kas iš dangaus ateina, Tas už visus viršesnis.
32ያየውንና የሰማውንም ይህን ይመሰክራል፥ ምስክሩንም የሚቀበለው የለም።
32Jis liudija, ką matė ir girdėjo, tik niekas Jo liudijimo nepriima.
33ምስክሩን የተቀበለ እግዚአብሔር እውነተኛ እንደ ሆነ አተመ።
33O kas Jo liudijimą priima, tas pripažįsta, jog Dievas teisus,
34እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራልና፤ እግዚአብሔር መንፈሱን ሰፍሮ አይሰጥምና።
34juk ką Dievas yra siuntęs, Tas kalba Dievo žodžius, nes Dievas teikia Dvasią be saiko.
35አባት ልጁን ይወዳል ሁሉንም በእጁ ሰጥቶታል።
35Tėvas myli Sūnų ir visa yra atidavęs į Jo rankas.
36በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም።
36Kas tiki Sūnų, turi amžinąjį gyvenimą, o kas netiki Sūnumi­gyvenimo nematys: ant jo pasilieka Dievo rūstybė.