1Po to Viešpats paskyrė dar kitus septyniasdešimt mokinių ir išsiuntė juos po du, kad eitų pirma Jo į visus miestus bei vietoves, kur Jis pats ketino vykti.
1ከዚህም በኋላ ጌታ ሌሎቹን ሰብዓ ሾመ፥ ሁለት ሁለትም አድርጎ እርሱ ሊሄድበት ወዳለው ከተማና ስፍራ ሁሉ በፊቱ ላካቸው።
2Jis sakė jiems: “Pjūtis tikrai didelė, o darbininkų maža. Todėl melskite pjūties Viešpatį, kad atsiųstų darbininkų į savo pjūtį.
2አላቸውም። መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዴህ የመከሩን ጌታ ለመከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት።
3Eikite! Štai Aš siunčiu jus lyg avinėlius tarp vilkų.
3ሂዱ፤ እነሆ፥ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ።
4Nesineškite nei piniginės, nei krepšio, nei sandalų ir nieko kelyje nesveikinkite.
4ኮረጆም ከረጢትም ጫማም አትያዙ፤ በመንገድም ለማንም እጅ አትንሡ።
5Į kuriuos tik namus užeisite, pirmiausia tarkite: ‘Ramybė šiems namams!’
5ወደምትገቡበት ቤት ሁሉ አስቀድማችሁ። ሰላም ለዚህ ቤት ይሁን በሉ።
6Ir jei ten bus ramybės sūnus, jūsų ramybė nužengs ant jo, o jei ne,sugrįš pas jus.
6በዚያም የሰላም ልጅ ቢኖር፥ ሰላማችሁ ያድርበታል፤ አለዚያም ይመለስላችኋል።
7Pasilikite tuose namuose, valgykite ir gerkite, kas duodama, nes darbininkas vertas savo užmokesčio. Nesikilnokite iš namų į namus.
7በዚያም ቤት ከእነርሱ ዘንድ ካለው እየበላችሁና እየጠጣችሁ ተቀመጡ፤ ለሠራተኛ ደመወዙ ይገባዋልና። ከቤት ወደ ቤት አትተላለፉ።
8Kai nueisite į kurį nors miestą ir jus priims, valgykite, kas bus jums padėta.
8ወደምትገቡባትም ከተማ ሁሉ ቢቀበሉአችሁ፥ ያቀረቡላችሁን ብሉ፤
9Gydykite jame esančius ligonius ir sakykite jiems: ‘Jums prisiartino Dievo karalystė!’
9በእርስዋም ያሉትን ድውዮችን ፈውሱና። የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ቀረበች በሉአቸው።
10O kai užeisite į tokį miestą, kur jūsų nepriims, išėję į gatves, sakykite:
10ነገር ግን ወደምትገቡባት ከተማ ሁሉ ባይቀበሉአችሁ፥ ወደ አደባባይዋ ወጥታችሁ።
11‘Mes nusikratome prieš jus net jūsų miesto dulkes, prilipusias prie mūsų kojų. Tačiau vis tiek žinokite: Dievo karalystė prisiartino prie jūsų!’
11ከከተማችሁ የተጣበቀብንን ትቢያ እንኳን እናራግፍላችኋለን፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ግን ወደ እናንተ እንደ ቀረበች ይህን እወቁ በሉ።
12Sakau jums: aną dieną Sodomai bus lengviau negu tam miestui.
12እላችኋለሁ፥ በዚያን ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶም ይቀልላታል።
13Vargas tau, Chorazine! Vargas tau, Betsaida! Jeigu Tyre ir Sidone būtų padaryta stebuklų, kokie padaryti pas jus, jie seniai būtų atgailavę, sėdėdami su ašutine ir pelenuose.
13ወዮልሽ ኮራዚን፥ ወዮልሽ ቤተ ሳይዳ፤ በእናንተ የተደረገው ተአምራት በጢሮስና በሲዶና ተደርጎ ቢሆን፥ ማቅ ለብሰው በአመድም ተቀምጠው ከብዙ ጊዜ በፊት ንስሐ በገቡ ነበር።
14Todėl Tyrui ir Sidonui teisme bus lengviau negu jums.
14ነገር ግን በፍርድ ከእናንተ ይልቅ ለጢሮስና ለሲዶና ይቀልላቸዋል።
15Ir tu, Kafarnaume, išaukštintas iki dangaus, nugarmėsi iki pragaro!
15አንቺም ቅፍርናሆም፥ እስከ ሰማይ ከፍ አልሽን? ወደ ሲኦል ትወርጃለሽ።
16Kas jūsų klauso, manęs klauso. Kas jus niekina, mane niekina. O kas niekina mane, niekina Tą, kuris mane siuntė”.
16የሚሰማችሁ እኔን ይሰማል፥ እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል፤ እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል።
17Septyniasdešimt sugrįžo, su džiaugsmu kalbėdami: “Viešpatie, mums paklūsta net demonai dėl Tavo vardo”.
17ሰብዓውም በደስታ ተመልሰው። ጌታ ሆይ፥ አጋንንት ስንኳ በስምህ ተገዝተውልናል አሉት።
18O Jis jiems sakė: “Mačiau šėtoną, kaip žaibą krintantį iš dangaus.
18እንዲህም አላቸው ሰይጣንን እንደ መብረቅ ከሰማይ ሲወድቅ አየሁ።
19Štai Aš duodu jums valdžią mindžioti gyvates bei skorpionus, aukštesnę už visą priešo jėgą, ir niekas jokiais būdais jums nepakenks.
19እነሆ፥ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ፥ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኋለሁ፥ የሚጐዳችሁም ምንም የለም።
20Bet jūs džiaukitės ne tuo, kad dvasios jums pavaldžios; džiaukitės, kad jūsų vardai įrašyti danguje”.
20ነገር ግን መናፍስት ስለ ተገዙላችሁ በዚህ ደስ አይበላችሁ፥ ስማችሁ ግን በሰማያት ሰለ ተጻፈ ደስ ይበላችሁ።
21Tą valandą Jėzus pradžiugo Dvasia ir tarė: “Aš šlovinu Tave, Tėve, dangaus ir žemės Viešpatie, kad paslėpei tai nuo išmintingųjų ir gudriųjų, o apreiškei mažutėliams. Taip, Tėve, nes Tau taip patiko.
21በዚያን ሰዓት ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ሐሤት አደረገና። የሰማይና የምድር ጌታ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና።
22Viskas man yra mano Tėvo atiduota. Ir niekas nežino, kas yra Sūnus, tik Tėvas, nei kas yra Tėvas, tik Sūnus ir tas, kam Sūnus nori apreikšti”.
22ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፥ ወልድንም ማን እንደ ሆነ ከአብ በቀር የሚያውቅ የለም፥ አብንም ማን እንደ ሆነ ከወልድ በቀር ወልድም ሊገልጥለት ከሚፈቅድ በቀር የሚያውቅ የለም አለ።
23Atsigręžęs vien tik į mokinius, Jis tarė: “Palaimintos akys, kurios regi, ką jūs regite.
23ወደ ደቀ መዛሙርቱም ዘወር ብሎ ለብቻቸው። የምታዩትን የሚያዩ ዓይኖች ብፁዓን ናቸው።
24Sakau jums: daugel pranašų ir karalių troško pamatyti, ką jūs matote, bet nepamatė, ir išgirsti, ką jūs girdite, bet neišgirdo”.
24እላችኋለሁና፥ እናንተ የምታዩትን ብዙዎች ነቢያትና ነገሥታት ሊያዩ ወደዱ አላዩምም፥ የምትሰሙትንም ሊሰሙ ወድደው አልሰሙም አለ።
25Štai atsistojo vienas Įstatymo mokytojas ir, mėgindamas Jį, paklausė: “Mokytojau, ką turiu daryti, kad paveldėčiau amžinąjį gyvenimą?”
25እነሆም፥ አንድ ሕግ አዋቂ ሊፈትነው ተነሥቶ። መምህር ሆይ፥ የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ? አለው።
26Jis tarė: “O kas parašyta Įstatyme? Kaip skaitai?”
26እርሱም በሕግ የተጻፈው ምንድር ነው? እንዴትስ ታነባለህ? አለው።
27Tas atsakė: “ ‘Mylėk Viešpatį, savo Dievą, visa savo širdimi, visa savo siela, visomis savo jėgomis ir visu savo protu, ir savo artimą kaip save patį’ ”.
27እርሱም መልሶ። ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም ኃይልህም በፍጹም አሳብህም ውደድ፥ ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ አለው።
28Jėzus jam tarė: “Gerai atsakei. Tai daryk, ir gyvensi”.
28ኢየሱስም። እውነት መለስህ፤ ይህን አድርግ በሕይወትም ትኖራለህ አለው።
29Norėdamas pateisinti save, anas paklausė Jėzų: “O kas gi mano artimas?”
29እርሱ ግን ራሱን ሊያጸድቅ ወድዶ ኢየሱስን። ባልንጀራዬስ ማን ነው? አለው።
30Jėzus atsakydamas tarė: “Vienas žmogus keliavo iš Jeruzalės į Jerichą ir pakliuvo į plėšikų rankas. Tie išrengė jį, sumušė ir nuėjo sau, palikdami pusgyvį.
30ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለ። አንድ ሰው ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ወረደ በወንበዴዎችም እጅ ወደቀ፤ እነርሱም ደግሞ ገፈፉት ደበደቡትም በሕይወትና በሞት መካከልም ትተውት ሄዱ።
31Atsitiktinai tuo pačiu keliu ėjo vienas kunigas ir, pamatęs jį, praėjo kita kelio puse.
31ድንገትም አንድ ካህን በዚያ መንገድ ወረደ አይቶትም ገለል ብሎ አለፈ።
32Taip pat ir levitas, pro tą vietą eidamas, jį pamatė ir praėjo kita kelio puse.
32እንዲሁም ደግሞ አንድ ሌዋዊ ወደዚያ ስፍራ መጣና አይቶት ገለል ብሎ አለፈ።
33O vienas samarietis keliaudamas užtiko jį ir pasigailėjo.
33አንድ ሳምራዊ ግን ሲሄድ ወደ እርሱ መጣ አይቶትም አዘነለት፥
34Priėjęs jis aprišo jo žaizdas, užpildamas aliejaus ir vyno, užkėlė ant savo gyvulio, nugabeno į užeigą ir slaugė jį.
34ቀርቦም ዘይትና የወይን ጠጅ በቍስሎቹ ላይ አፍስሶ አሰራቸው፥ በራሱ አህያም ላይ አስቀምጦት ወደ እንግዶች ማደርያ ወሰደው ጠበቀውም።
35Kitą dieną iškeliaudamas jis išsiėmė du denarus, padavė užeigos šeimininkui ir tarė: ‘Slaugyk jį, o jeigu ką išleisi viršaus, sugrįžęs atsilyginsiu’.
35በማግሥቱም ሁለት ዲናር አውጥቶ ለባለቤቱ ሰጠና። ጠብቀው፥ ከዚህም በላይ የምትከስረውን ሁሉ እኔ ስመለስ እከፍልሃለሁ አለው።
36Kas iš šitų trijų tau atrodo buvęs artimas patekusiam į plėšikų rankas?”
36እንግዲህ ከነዚህ ከሦስቱ በወንበዴዎች እጅ ለወደቀው ባልንጀራ የሆነው ማንኛው ይመስልሃል?
37Jis atsakė: “Tas, kuris jo pasigailėjo”. Jėzus jam tarė: “Eik ir tu taip daryk!”
37እርሱም። ምሕረት ያደረገለት አለ። ኢየሱስም። ሂድ አንተም እንዲሁ አድርግ አለው።
38Jiems keliaujant toliau, Jėzus užsuko į vieną kaimą. Ten viena moteris, vardu Morta, pakvietė Jį į savo namus.
38ሲሄዱም እርሱ ወደ አንዲት መንደር ገባ፤ ማርታ የተባለች አንዲት ሴትም በቤትዋ ተቀበለችው።
39Ji turėjo seserį, vardu Marija. Ši, atsisėdusi prie Viešpaties kojų, klausėsi Jo žodžių.
39ለእርስዋም ማርያም የምትባል እኅት ነበረቻት፥ እርስዋም ደግሞ ቃሉን ልትሰማ በኢየሱስ እግር አጠገብ ተቀምጣ ነበረች።
40O Morta rūpinosi visokiu patarnavimu ir stabtelėjusi pasiskundė: “Viešpatie, Tau nerūpi, kad sesuo palieka mane vieną patarnauti? Pasakyk jai, kad man padėtų”.
40ማርታ ግን አገልግሎት ስለ በዛባት ባከነች፤ ቀርባም። ጌታ ሆይ፥ እኔ እንድሠራ እኅቴ ብቻዬን ስትተወኝ አይገድህምን? እንኪያስ እንድታግዘኝ ንገራት አለችው።
41Tačiau Viešpats atsakė: “Morta, Morta, tu rūpiniesi ir nerimauji dėl daugelio dalykų,
41ኢየሱስም መልሶ። ማርታ፥ ማርታ፥ በብዙ ነገር ትጨነቂአለሽ ትታወኪማለሽ፥
42o tereikia vieno. Marija išsirinko geriausiąją dalį, kuri nebus iš jos atimta”.
42የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት።