1Kartą Jėzus vienoje vietoje meldėsi. Jam baigus melstis, vienas iš Jo mokinių paprašė: “Viešpatie, išmokyk mus melstis, kaip ir Jonas išmokė savo mokinius”.
1እርሱም በአንድ ስፍራ ይጸልይ ነበር፥ በጨረሰም ጊዜ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ። ጌታ ሆይ፥ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርቱን እንዳስተማረ እንጸልይ ዘንድ አስተምረን አለው።
2Jėzus tarė jiems: “Kai meldžiatės, sakykite: ‘Tėve mūsų, kuris esi danguje, teesie šventas Tavo vardas. Teateinie Tavo karalystė. Tebūnie Tavo valia kaip danguje, taip ir žemėje.
2አላቸውም። ስትጸልዩ እንዲህ በሉ። በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፤ ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤
3Kasdienės mūsų duonos duok mums kasdien
3የዕለት እንጀራችንን ዕለት ዕለት ስጠን፤
4ir atleisk mums mūsų kaltes, nes ir mes atleidžiame kiekvienam, kuris mums kaltas. Ir nevesk mūsų į pagundymą, bet gelbėk mus nuo pikto’ ”.
4ኃጢአታችንንም ይቅር በለን፥ እኛ ደግሞ የበደሉንን ሁሉ ይቅር ብለናልና፤ ከክፉ አድነን እንጂ ወደ ፈተና አታግባን።
5Jis kalbėjo jiems: “Kas nors iš jūsų turės draugą ir, nuėjęs pas jį vidurnaktį, sakys: ‘Bičiuli, paskolink man tris kepalus duonos,
5እንዲህም አላቸው። ከእናንተ ማናቸውም ወዳጅ ያለው፥ በእኩል ሌሊትስ ወደ እርሱ ሄዶ። ወዳጄ ሆይ፥ ሦስት እንጀራ አበድረኝ፥
6nes draugas iš kelionės pas mane atvyko ir neturiu ko jam padėti ant stalo’.
6አንድ ወዳጄ ከመንገድ ወደ እኔ መጥቶ የማቀርብለት የለኝምና ይላልን?
7O anas iš vidaus atsilieps: ‘Nekvaršink manęs! Durys jau uždarytos, o aš su vaikais lovoje, negaliu keltis ir tau duoti’.
7ያም ከውስጥ መልሶ። አታድክመኝ፤ አሁን ደጁ ተቈልፎአል ልጆቼም ከእኔ ጋር በአልጋ ላይ አሉ፤ ተነሥቼ ልሰጥህ አልችልም ይላልን?
8Aš jums sakau: jeigu nesikels ir neduos jam duonos dėl draugystės, tai dėl jo atkaklumo atsikels ir duos, kiek tik jam reikia.
8እላችኋለሁ፥ ወዳጅ ስለ ሆነ ተነሥቶ ባይሰጠው እንኳ፥ ስለ ንዝነዛው ተነስቶ የሚፈልገውን ሁሉ ይሰጠዋል።
9Tad ir Aš jums sakau: prašykite, ir jums bus duota; ieškokite, ir rasite; belskite, ir bus jums atidaryta.
9እኔም እላችኋለሁ። ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፍትላችሁማል።
10Nes kiekvienas, kas prašo, gauna, kas ieško, randa, ir beldžiančiam atidaroma.
10የሚለምን ሁሉ ይቀበላልና፥ የሚፈልግም ያገኛል፥ መዝጊያውንም ለሚያንኳኳው ይከፈትለታል።
11Kuris iš jūsų, būdamas tėvas, duonos prašančiam vaikui duotų akmenį?! Ar prašančiam žuvies duotų gyvatę?
11አባት ከሆናችሁ ከእናንተ ከማንኛችሁም ልጁ እንጀራ ቢለምነው፥ እርሱም ድንጋይ ይሰጠዋልን? ዓሣ ደግሞ ቢለምነው በዓሣ ፋንታ እባብ ይሰጠዋልን?
12Arba prašančiam kiaušinio duotų skorpioną?
12ወይስ እንቍላል ቢለምነው ጊንጥ ይሰጠዋልን?
13Jei tad jūs, būdami blogi, mokate savo vaikams duoti gerų daiktų, juo labiau jūsų Tėvas iš dangaus duos Šventąją Dvasią tiems, kurie Jį prašo”.
13እንኪያስ እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠት ካወቃችሁ፥ በሰማይ ያለው አባት ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መንፈስ ቅዱስን ይሰጣቸው?
14Kartą Jėzus išvarė nebylumo demoną. Demonui išėjus, nebylys prakalbėjo, ir minios stebėjosi.
14ዲዳውንም ጋኔን ያወጣ ነበር፤ ጋኔኑም ከወጣ በኋላ ዲዳው ተናገረ ሕዝቡም ተደነቁ፤
15Bet kai kurie iš jų sakė: “Jis išvaro demonus demonų valdovo Belzebulo jėga”.
15ነገር ግን ከእነርሱ አንዳንዱ። በብዔል ዜቡል በአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያወጣል አሉ።
16Kiti, mėgindami Jį, reikalavo ženklo iš dangaus.
16ሌሎችም ሲፈትኑት ከሰማይ ምልክት ከእርሱ ይፈልጉ ነበር።
17Bet Jėzus, žinodamas jų mintis, tarė jiems: “Kiekviena suskilusi karalystė bus sunaikinta, ir namai grius ant namų.
17እርሱ ግን አሳባቸውን አውቆ እንዲህ አላቸው። እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁሉ ትጠፋለች፤ ቤትም በቤት ላይ ይወድቃል።
18Jeigu ir šėtonas pasidalijęs, tai kaip išsilaikys jo karalystė? O jūs sakote, kad Aš išvarau demonus Belzebulo jėga.
18እኔ አጋንንትን በብዔል ዜቡል እንዳወጣ ትላላችሁና ሰይጣን ደግሞ እርስ በርሱ ከተለያየ መንግሥቱ እንዴት ትቆማለች?
19Jeigu Aš išvarau juos Belzebulo jėga, tai kieno jėga išvaro jūsų sūnūs? Todėl jie bus jūsų teisėjai.
19እኔስ በብዔል ዜቡል አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ ልጆቻችሁ በማን ያወጡአቸዋል? ስለዚህ እነርሱ ፈራጆች ይሆኑባችኋል።
20Bet jei Aš išvarau demonus Dievo pirštu, tai tikrai pas jus atėjo Dievo karalystė.
20እኔ ግን በእግዚአብሔር ጣት አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ እንግዲህ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ደርሳለች።
21Kai apsiginklavęs galiūnas saugo savo namus, tada ir jo turtas apsaugotas.
21ኃይለኛ ሰው ጋሻና ጦር ይዞ የራሱን ግቢ ቢጠብቅ፥ ያለው ገንዘቡ በሰላም ይሆናል፤
22Bet jei užpuls stipresnis ir jį nugalės, tai atims visus jo ginklus, kuriais tas pasitikėjo, ir išdalys grobį.
22ከእርሱ ይልቅ የሚበረታ መጥቶ ሲያሸንፈው ግን፥ ታምኖበት የነበረውን ጋሻና ጦር ይወስድበታል ምርኮውንም ያካፍላል።
23Kas ne su manimi, tas prieš mane, ir kas nerenka su manimi, tas barsto”.
23ከእኔ ጋር ያልሆነ ይቃወመኛል፥ ከእኔ ጋርም የማያከማች ይበትናል።
24“Netyroji dvasia, išėjusi iš žmogaus, klaidžioja bevandenėse vietose, ieškodama poilsio. Neradusi ji sako: ‘Grįšiu į savo namus, iš kur išėjau’.
24ርኵስ መንፈስ ከሰው በወጣ ጊዜ ዕረፍትን እየፈለገ ውኃ በሌለበት ቦታ ያልፋል፤ ባያገኝም። ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል፤
25Sugrįžusi randa juos iššluotus ir išpuoštus.
25ሲመጣም ተጠርጎ አጊጦም ያገኘዋል።
26Tuomet eina, pasiima kitas septynias dvasias, dar piktesnes už save, ir įėjusios jos ten apsigyvena. Ir tada tam žmogui darosi blogiau negu pirma”.
26ከዚያ ወዲያ ይሄድና ከእርሱ የከፉትን ሌሎችን ሰባት አጋንንት ከእርሱ ጋር ይይዛል፥ ገብተውም በዚያ ይኖራሉ፤ ለዚያም ሰው ከፊተኛው ይልቅ የኋለኛው ይብስበታል።
27Jėzui bekalbant, viena moteris iš minios Jam garsiai sušuko: “Palaimintos įsčios, kurios Tave nešiojo, ir krūtys, kurias žindai!”
27ይህንም ሲናገር፥ ከሕዝቡ አንዲት ሴት ድምፅዋን ከፍ አድርጋ። የተሸከመችህ ማኅፀንና የጠባሃቸው ጡቶች ብፁዓን ናቸው አለችው።
28Jis atsiliepė: “Labiau palaiminti tie, kurie klausosi Dievo žodžio ir jo laikosi”.
28እርሱ ግን። አዎን፥ ብፁዓንስ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚጠብቁት ናቸው አለ።
29Minioms gausėjant, Jis pradėjo kalbėti: “Ši karta yra pikta karta. Ji reikalauja ženklo, bet jai nebus duota jokio kito ženklo, kaip tik Jonos ženklas.
29ብዙ ሕዝብም በተሰበሰቡ ጊዜ እንዲህ ይል ጀመር። ይህ ትውልድ ክፉ ነው፤ ምልክት ይፈልጋል፥ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም።
30Kaip Jona buvo ženklas nineviečiams, taip Žmogaus Sūnus bus šiai kartai.
30ዮናስ ለነነዌ ሰዎች ምልክት እንደ ሆናቸው፥ እንዲሁ ደግሞ የሰው ልጅ ለዚህ ትውልድ ምልክት ይሆናል።
31Pietų šalies karalienė teismo dieną prisikels drauge su šios kartos žmonėmis ir juos pasmerks, nes ji atkeliavo nuo žemės pakraščių pasiklausyti Saliamono išminties, o štai čia daugiau negu Saliamonas.
31ንግሥተ አዜብ በፍርድ ከዚህ ትውልድ ሰዎች ጋር ተነሥታ ትፈርድባቸዋለች፤ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና፥ እነሆም፥ ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ።
32Ninevės gyventojai stos teisme drauge su šita karta ir ją pasmerks, nes jie atsivertė, išgirdę Jonos pamokslą, o čia daugiau negu Jona”.
32የነነዌ ሰዎች በፍርድ ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፥ እነሆም፥ ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ።
33“Niekas uždegto žiburio nededa į slėptuvę ar po indu, bet stato jį į žibintuvą, kad įeinantys matytų šviesą.
33መብራትንም አብርቶ በስውር ወይም በእንቅብ በታች የሚያኖረው የለም፥ የሚገቡ ሰዎች ብርሃኑን እንዲያዩ በመቅረዝ ላይ ያኖረዋል እንጂ።
34Kūno žiburys yra tavoji akis. Todėl, jei tavo akis sveika, visas tavo kūnas bus šviesus. O jeigu tavo akis pikta, visas tavo kūnas bus tamsus.
34የሰውነትህ መብራት ዓይንህ ናት። ዓይንህ ጤናማ በሆነች ጊዜ ሰውነትህ ሁሉ ደግሞ ብሩህ ይሆናል። ዓይንህ ታማሚ በሆነች ጊዜ ግን ሰውነትህ ደግሞ የጨለመ ይሆናል።
35Todėl žiūrėk, kad tavoji šviesa nebūtų tamsa!
35እንግዲህ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ እንዳይሆን ተመልከት።
36Taigi, jei visas tavo kūnas pilnas šviesos ir neturi jokios tamsios dalies, jis bus visas šviesus, lyg žiburio spindulių apšviestas”.
36እንግዲህ ሰውነትህ ሁሉ የጨለማ ቍራጭ የሌለበት ብሩህ ቢሆን፥ መብራት በደመቀ ብርሃን እንደሚያበራልህ በጭራሽ ብሩህ ይሆናል።
37Jėzui tebekalbant, vienas fariziejus pasikvietė Jį pietų. Įėjęs į vidų, Jis atsisėdo prie stalo.
37ይህንንም ሲናገር አንድ ፈሪሳዊ ከእርሱ ጋር ምሳ ይበላ ዘንድ ለመነው ገብቶም ተቀመጠ።
38Tai matydamas, fariziejus stebėjosi, kad Jis nenusiplovė rankų prieš valgydamas.
38ከምሳም በፊት አስቀድሞ እንዳልታጠበ ባየው ጊዜ ፈሪሳዊው ተደነቀ።
39O Viešpats jam tarė: “Kaip tik jūs, fariziejai, valote taurės ir dubens išorę, o viduje esate pilni gobšumo ir nedorybės.
39ጌታም እንዲህ አለው። አሁን እናንተ ፈሪሳውያን የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ታጠራላችሁ፥ ውስጣችሁ ግን ቅሚያና ክፋት ሞልቶበታል
40Neišmanėliai! Argi išorės Kūrėjas nesukūrė ir vidaus?
40እናንት ደንቆሮዎች፥ የውጭውን የፈጠረ የውስጡን ደግሞ አልፈጠረምን?
41Verčiau duokite gailestingumo auką iš to, ką turite, tai viskas bus jums nesutepta.
41ነገር ግን በውስጥ ያለውን ምጽዋት አድርጋችሁ ስጡ፥ እነሆም፥ ሁሉ ንጹሕ ይሆንላችኋል።
42Vargas jums, fariziejai! Jūs duodate dešimtinę iš mėtų, rūtų ir kitokių žolelių, o apleidžiate teisingumą ir Dievo meilę. Tai turite daryti ir ano nepalikti!
42ነገር ግን እናንተ ፈሪሳውያን፥ ከአዝሙድና ከጤና አዳም ከአትክልትም ሁሉ አሥራት ስለምታወጡ፥ ፍርድንና እግዚአብሔርን መውደድ ስለምትተላለፉ፥ ወዮላችሁ፤ ነገር ግን ሌላውን ሳትተዉ ይህን ልታደርጉት ይገባችሁ ነበር።
43Vargas jums, fariziejai! Jūs mėgstate pirmuosius krėslus sinagogose ir sveikinimus aikštėse.
43እናንተ ፈሪሳውያን፥ በምኵራብ የከበሬታ ወንበር በገበያም ሰላምታ ስለምትወዱ፥ ወዮላችሁ።
44Vargas jums, veidmainiai Rašto žinovai ir fariziejai! Esate lyg apleisti kapai, kuriuos žmonės nepastebėdami mindžioja”.
44እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ ሰዎች ሳያውቁ በላዩ የሚሄዱበት የተሰወረ መቃብር ስለምትመስሉ፥ ወዮላችሁ።
45Tada vienas Įstatymo mokytojas atsiliepė: “Mokytojau, taip kalbėdamas, Tu ir mus įžeidi”.
45ከሕግ አዋቂዎችም አንዱ መልሶ። መምህር ሆይ፥ ይህን ማለትህ እኛን ደግሞ መስደብህ ነው አለው።
46Jis atsakė: “Vargas ir jums, Įstatymo mokytojai! Jūs kraunate žmonėms nepakeliamas naštas, o patys tų naštų nė vienu pirštu nepajudinate.
46እርሱም እንዲህ አለ። እናንተ ደግሞ ሕግ አዋቂዎች፥ አስቸጋሪ ሸክም ለሰዎች ስለምታሸክሙ፥ ራሳችሁም በአንዲት ጣታችሁ ስንኳ ሸክሙን ስለማትነኩት፥ ወዮላችሁ።
47Vargas jums! Jūs statote pranašams antkapius, o jūsų tėvai juos žudė!
47አባቶቻችሁ የገደሉአቸውን የነቢያትን መቃብር ስለምትሠሩ፥ ወዮላችሁ።
48Taigi jūs liudijate, kad pritariate savo tėvų darbams. Jie žudė, o jūs statote jiems antkapius.
48እንግዲህ ለአባቶቻችሁ ሥራ ትመሰክራላችሁ ትስማማላችሁም፤ እነርሱ ገድለዋቸዋልና፥ እናንተም መቃብራቸውን ትሠራላችሁ።
49Todėl ir Dievo išmintis pasakė: ‘Aš siųsiu pas juos pranašų ir apaštalų, o jie vienus nužudys, kitus persekios,
49ስለዚህ ደግሞ የእግዚአብሔር ጥበብ እንዲህ አለች። ወደ እነርሱ ነቢያትንና ሐዋርያትን እልካለሁ፥ ከእነርሱም ይገድላሉ ያሳድዱማል፥
50kad iš šitos kartos būtų pareikalauta visų pranašų kraujo, pralieto nuo pasaulio sutvėrimo,
50ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የፈሰሰው የነቢያት ሁሉ ደም፥
51pradedant Abelio krauju iki kraujo Zacharijo, kuris buvo nužudytas tarp aukuro ir šventyklos!’ Taip! Aš sakau, jog bus pareikalauta jo iš šios kartos.
51ከአቤል ደም ጀምሮ በመሠዊያውና በቤተ መቅደስ መካከል እስከ ጠፋው እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ፥ ከዚህ ትውልድ እንዲፈለግ አዎን እላችኋለሁ፥ ከዚህ ትውልድ ይፈለጋል።
52Vargas jums, Įstatymo mokytojai! Jūs paėmėte pažinimo raktą, bet patys nėjote ir einantiems trukdėte”.
52እናንተ ሕግ አዋቂዎች፥ የእውቀትን መክፈቻ ስለ ወሰዳችሁ፥ ወዮላችሁ ራሳችሁ አልገባችሁም የሚገቡትንም ከለከላችሁ።
53Kai Jis jiems tai kalbėjo, Rašto žinovai bei fariziejai pradėjo smarkiai Jį pulti ir visaip kamantinėti,
53ይህንም ሲናገራቸው፥ ጻፎችና ፈሪሳውያን በአፉ የተናገረውን ሊነጥቁ ሲያደቡ፥ እጅግ ይቃወሙና ስለ ብዙ ነገር እንዲናገር ያነሣሡ ጀመር።
54tikėdamiesi ką nors pagauti iš Jo lūpų, kad galėtų Jį apkaltinti.