1Tuo tarpu, kai susirinko nesuskaičiuojama minia, kad net vieni kitus trypė, Jėzus pradėjo kalbėti pirmiausia savo mokiniams: “Saugokitės fariziejų raugo, tai yra veidmainystės!
1በዚያን ጊዜ የሕዝብ አእላፍ እርስ በርሳቸው እስኪረጋገጡ ድረስ ተሰብስበው ሳሉ፥ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ይል ጀመር። አስቀድማችሁ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ፥ እርሱም ግብዝነት ነው።
2Nėra nieko uždengto, kas nebus atidengta, ir nieko paslėpto, kas nepasidarys žinoma.
2ነገር ግን የማይገለጥ የተከደነ፥ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለም።
3Todėl ką kalbėjote tamsoje, skambės šviesoje, ir ką šnibždėjote į ausį kambariuose, bus skelbiama nuo stogų.
3ስለዚህ በጨለማ የምትናገሩት ሁሉ በብርሃን ይሰማል፥ በእልፍኝም ውስጥ በጆሮ የምትናገሩት በሰገነት ላይ ይሰበካል።
4Sakau jums, savo draugams: nebijokite tų, kurie žudo kūną ir paskui nebegali daugiau nieko padaryti.
4ለእናንተም ለወዳጆቼ እላችኋለሁ፥ ሥጋን የሚገድሉትን በኋላም አንድ ስንኳ የሚበልጥ ሊያደርጉ የማይችሉትን አትፍሩ።
5Aš parodysiu jums, ko turite bijoti: bijokite to, kuris nužudęs, turi galią įmesti į pragarą. Taip, sakau jums, šito bijokite!
5እኔ ግን የምትፈሩትን አሳያችኋለሁ፤ ከገደለ በኋላ ወደ ገሃነም ለመጣል ሥልጣን ያለውን ፍሩ። አዎን እላችኋለሁ፥ እርሱን ፍሩ።
6Argi ne penki žvirbliai parduodami už du skatikus? Tačiau nė vienas iš jų nėra Dievo pamirštas.
6አምስት ድንቢጦች በአሥር ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ከእነርሱም አንዲቱ ስንኳ በእግዚአብሔር ፊት አትረሳም።
7O jūsų net visi galvos plaukai suskaičiuoti. Tad nebijokite! Jūs vertesni už daugybę žvirblių.
7ነገር ግን የእናንተ የራሳችሁ ጠጕር ሁሉ እንኳ የተቈጠረ ነው፤ እንግዲያስ አትፍሩ ከብዙ ድንቢጦች ትበልጣላችሁ።
8Aš jums sakau: kas išpažins mane žmonių akivaizdoje, tą Žmogaus Sūnus išpažins Dievo angelų akivaizdoje.
8እላችሁማለሁ፥ በሰው ፊት የሚመሰክርልኝ ሁሉ፥ የሰው ልጅ ደግሞ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ይመሰክርለታል፤
9O kas manęs išsigins žmonių akivaizdoje, to bus išsiginta Dievo angelų akivaizdoje.
9በሰውም ፊት የሚክደኝ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ይካዳል።
10Kas tars žodį prieš Žmogaus Sūnų, tam bus atleista, o kas piktžodžiaus Šventajai Dvasiai, tam nebus atleista.
10በሰው ልጅም ላይ ቃል የሚናገር ሁሉ ይሰረይለታል፤ መንፈስ ቅዱስን የሚሰድብ ግን አይሰረይለትም።
11Kai jie ves jus į sinagogas, pas valdininkus ar vyresnybes, nesirūpinkite, kaip ar ką atsakysite ir ką kalbėsite,
11ወደ ምኵራቦችና ወደ መኳንንቶችም ወደ ገዢዎችም ሲጐትቱአችሁ፥ እንዴት ወይም ምን እንድትመልሱ ወይም እንድትናገሩ አትጨነቁ፤
12nes Šventoji Dvasia tą pačią valandą pamokys jus, ką kalbėti”.
12መንፈስ ቅዱስ በዚያች ሰዓት ልትናገሩ የሚገባችሁን ያስተምራችኋልና።
13Vienas iš minios Jam tarė: “Mokytojau, liepk mano broliui, kad pasidalytų su manimi palikimą”.
13ከሕዝቡም አንድ ሰው። መምህር ሆይ፥ ርስቱን ከእኔ ጋር እንዲካፈል ለወንድሜ ንገረው አለው።
14Jis atsakė: “Žmogau, kas gi mane skyrė jūsų teisėju ar dalytoju?”
14እርሱም። አንተ ሰው፥ ፈራጅና አካፋይ በላያችሁ አንድሆን ማን ሾመኝ? አለው።
15Jis pasakė jiems: “Žiūrėkite, saugokitės godumo, nes žmogaus gyvybė nepriklauso nuo jo turto gausos”.
15የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለምና ተጠንቀቁ፥ ከመጐምጀትም ሁሉ ተጠበቁ አላቸው።
16Jis pasakė jiems palyginimą: “Vieno turtingo žmogaus laukai davė gausų derlių.
16ምሳሌም ነገራቸው እንዲህ ሲል። አንድ ባለ ጠጋ ሰው እርሻ እጅግ ፍሬያም ሆነችለት።
17Jis ėmė sau vienas svarstyti: ‘Ką man dabar daryti? Neturiu kur sukrauti derliaus’.
17እርሱም። ፍሬዬን የማከማችበት ስፍራ አጥቻለሁና ምን ላድርግ? ብሎ በልቡ አሰበ።
18Pagaliau jis tarė: ‘Štai ką padarysiu: nugriausiu savo klojimus, statysiuos didesnius ir į juos sugabensiu visus javus ir visas gėrybes.
18እንዲህ አደርጋለሁ፤ ጐተራዬን አፍርሼ ሌላ የሚበልጥ እሠራለሁ፥ በዚያም ፍሬዬንና በረከቴን ሁሉ አከማቻለሁ፤
19Tuomet sakysiu savo sielai: ‘Siela, tu turi daug gėrybių, sukrautų ilgiems metams. Ilsėkis, valgyk, gerk ir linksminkis!’
19ነፍሴንም። አንቺ ነፍሴ፥ ለብዙ ዘመን የሚቀር ብዙ በረከት አለሽ፤ ዕረፊ፥ ብዪ፥ ጠጪ፥ ደስ ይበልሽ እላታለሁ አለ።
20O Dievas jam tarė: ‘Kvaily, dar šiąnakt bus pareikalauta tavo sielos. Kam gi atiteks, ką susikrovei?’
20እግዚአብሔር ግን። አንተ ሰነፍ፥ በዚች ሌሊት ነፍስህን ከአንተ ሊወስዱአት ይፈልጓታል፤ ይህስ የሰበሰብኸው ለማን ይሆናል? አለው።
21Taip yra tam, kuris krauna turtus sau, bet nesirūpina tapti turtingas pas Dievą”.
21ለራሱ ገንዘብ የሚያከማች፥ በእግዚአብሔር ዘንድም ባለ ጠጋ ያልሆነ እንዲህ ነው።
22Tada Jėzus kalbėjo savo mokiniams: “Todėl sakau jums: nesirūpinkite savo gyvybe, ką valgysite, nė kūnu, ką vilkėsite.
22ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ። ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ለነፍሳችሁ በምትበሉት ወይም ለሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ።
23Gyvybė svarbesnė už maistą, o kūnas už drabužį.
23ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ ይበልጣልና።
24Įsižiūrėkite į varnus. Jie nei sėja, nei pjauna, neturi nei sandėlių, nei kluonų, ir Dievas juos maitina. Jūs nepalyginamai vertesni už paukščius!
24ቍራዎችን ተመልከቱ፤ አይዘሩም አያጭዱምም፥ ዕቃ ቤትም ወይም ጎተራ የላቸውም፥ እግዚአብሔርም ይመግባቸዋል፤ እናንተስ ከወፎች እንዴት ትበልጣላችሁ?
25Kas gi iš jūsų galėtų savo rūpesčiu bent per sprindį pridėti sau ūgio?
25ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማን ነው?
26Jei tad jūs nesugebate padaryti net mažmožio, tai kam rūpinatės kitais dalykais?
26እንግዲህ ትንሹን ነገር ስንኳ የማትችሉ ከሆናችሁ፥ ስለ ምን በሌላ ትጨነቃላችሁ?
27Įsižiūrėkite, kaip auga lelijos. Jos nesidarbuoja ir neaudžia, bet sakau jums: nė Saliamonas visoje savo šlovėje nebuvo taip pasipuošęs kaip kiekviena iš jų.
27አበቦችን እንዴት እንዲያድጉ ተመልከቱ፤ አይደክሙም አይፈትሉምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከእነዚህ እንደ አንዲቱ አለበሰም።
28Jeigu Dievas taip aprengia laukų žolę, šiandien žaliuojančią, o rytoj metamą į krosnį, tai dar labiau pasirūpins jumis, mažatikiai!
28እግዚአብሔር ግን ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን በሜዳ የሆነውን ሣር እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ፥ እናንተ እምነት የጐደላችሁ፥ እናንተንማ ይልቁን እንዴት?
29Ir neklausinėkite, ką valgysite ar gersite, ir nesirūpinkite!
29እናንተም የምትበሉትን የምትጠጡትንም አትፈልጉ፥ አታወላውሉም፤
30Visų tų dalykų ieško šio pasaulio pagonys. O jūsų Tėvas žino, kad viso to jums reikia.
30ይህንስ ሁሉ በዓለም ያሉ አሕዛብ ይፈልጉታልና፤ የእናንተም አባት ይህ እንዲያስፈልጋችሁ ያውቃል።
31Verčiau ieškokite Jo karalystės, o visa tai bus jums pridėta.
31ዳሩ ግን መንግሥቱን ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።
32Nebijok, mažoji kaimene: jūsų Tėvas panorėjo duoti jums karalystę!”
32አንተ ታናሽ መንጋ፥ መንግሥትን ሊሰጣችሁ የአባታችሁ በጎ ፈቃድ ነውና አትፍሩ።
33“Parduokite savo turtą ir aukokite gailestingumo aukas. Įsitaisykite sau piniginių, kurios nesusidėvi, kraukite nenykstantį turtą danguje, kur joks vagis neprieina ir kandys nesuėda.
33ያላችሁን ሽጡ ምጽዋትም ስጡ፤ ሌባ በማይቀርብበት ብልም በማያጠፋበት በሰማያት የማያልቅ መዝገብ የሚሆኑትን የማያረጁትንም ኮረጆዎች ለራሳችሁ አድርጉ፤
34Nes kur jūsų turtas, ten ir jūsų širdis”.
34መዝገባችሁ ባለበት ልባችሁ ደግሞ በዚያ ይሆናልና።
35“Tebūna jūsų strėnos sujuostos ir žiburiai uždegti,
35ወገባችሁ የታጠቀ መብራታችሁም የበራ ይሁን፤
36ir būkite panašūs į žmones, kurie laukia savo šeimininko, grįžtančio iš vestuvių, kad kai tik jis parvyks ir pasibels, tuojau atidarytų.
36እናንተም ጌታቸው መጥቶ ደጁን ሲያንኳኳ ወዲያው እንዲከፍቱለት ከሰርግ እስኪመለስ ድረስ የሚጠብቁ ሰዎችን ምሰሉ
37Palaiminti tie tarnai, kuriuos sugrįžęs šeimininkas ras budinčius. Iš tiesų sakau jums: jis susijuos, susodins juos prie stalo ir priėjęs patarnaus jiems.
37ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።
38Jeigu jis grįžtų antrosios ar trečiosios nakties sargybos metu ir rastų juos budinčius, palaiminti tie tarnai!
38ከሌሊቱም በሁለተኛው ወይም በሦስተኛው ክፍል መጥቶ እንዲሁ ቢያገኛቸው፥ እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው።
39Įsidėmėkite: jei šeimininkas žinotų, kurią valandą ateis vagis, budėtų ir neleistų jam įsilaužti į savo namus.
39ይህን ግን እወቁ ባለቤት በምን ሰዓት ሌባ እንዲመጣ ቢያውቅ ኖሮ፥ በነቃ፥ ቤቱም እንዲቆፈር ባልፈቀደም ነበር።
40Todėl ir jūs būkite pasirengę, nes Žmogaus Sūnus ateis tą valandą, kurią nesitikėsite”.
40እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።
41Tada Petras paklausė: “Viešpatie, ar šį palyginimą sakai tik mums, ar visiems?”
41ጴጥሮስም። ጌታ ሆይ፥ ይህን ምሳሌ ለእኛ ወይስ ደግሞ ለሁሉ ትናገራለህን? አለው።
42Viešpats atsakė: “Kas yra tas ištikimas ir sumanus ūkvedys, kurį šeimininkas paskirs vadovauti šeimynai ir deramu laiku duoti jiems skirtą maisto dalį?
42ጌታም አለ። እንኪያስ ምግባቸውን በጊዜው ይሰጣቸው ዘንድ ጌታው በቤተ ሰዎቹ ላይ የሚሾመው ታማኝና ልባም መጋቢ ማን ነው?
43Palaimintas tarnas, kurį sugrįžęs šeimininkas ras taip darantį.
43ጌታው መጥቶ እንዲህ ሲያደርግ የሚያገኘው ያ ባሪያ ብፁዕ ነው።
44Sakau jums tiesą: jis paskirs jį valdyti visų savo turtų.
44እውነት እላችኋለሁ፥ ባለው ሁሉ ላይ ይሾመዋል።
45Bet jeigu anas tarnas tartų savo širdyje: ‘Mano šeimininkas neskuba grįžti’, ir imtų mušti tarnus bei tarnaites, valgyti, gerti ir girtuokliauti,
45ያ ባሪያ ግን። ጌታዬ እስኪመጣ ይዘገያል ብሎ በልቡ ቢያስብ ሎሌዎችንና ገረዶችንም ይመታ ይበላም ይጠጣም ይሰክርም ዘንድ ቢጀምር፥
46tai to tarno šeimininkas sugrįš tą dieną, kai jis nelaukia, ir tą valandą, kurią jis nesitiki. Jis perkirs jį pusiau ir paskirs jam dalį su neištikimaisiais.
46የዚያ ባሪያ ጌታ ባልጠበቃት ቀን ባላወቃትም ሰዓት ይመጣል፥ ከሁለትም ይሰነጥቀዋል እድሉንም ከማይታመኑ ጋር ያደርጋል።
47Tarnas, kuris žino savo šeimininko valią, bet nėra pasiruošęs ir pagal jo valią nedaro, bus smarkiai nuplaktas.
47የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ያ ባሪያ እጅግ ይገረፋል፤
48O kuris nežino ir baustinai elgiasi, bus mažai plakamas. Iš kiekvieno, kuriam daug duota, bus daug pareikalauta, ir kam daug patikėta, iš to bus daug ir išieškota”.
48ያላወቀ ግን መገረፍ የሚገባውንም ያደረገ ጥቂት ይገረፋል። ብዙም ከተሰጠው ሰው ሁሉ ከእርሱ ብዙ ይፈለግበታል፥ ብዙ አደራም ከተሰጠው ከእርሱ አብዝተው ይሹበታል።
49“Aš atėjau uždegti žemėje ugnies ir taip noriu, kad ji jau liepsnotų!
49በምድር ላይ እሳት ልጥል መጣሁ፥ አሁንም የነደደ ከሆነ ዘንድ ምን እፈልጋለሁ?
50Bet Aš turiu būti pakrikštytas krikštu ir kaip esu slegiamas, kol tai išsipildys!”
50ነገር ግን የምጠመቃት ጥምቀት አለችኝ፥ እስክትፈጸምም ድረስ እንዴት እጨነቃለሁ?
51“Gal manote, kad atėjau atnešti žemėn ramybės? Ne, sakau jums, ne ramybės, o nesantaikos.
51በምድር ላይ ሰላምንም ለመስጠት የመጣሁ ይመስላችኋልን? እላችኋለሁ፥ አይደለም፥ መለያየትን እንጂ።
52Nuo dabar penki vienuose namuose bus pasidaliję: trys prieš du ir du prieš tris.
52ከአሁን ጀምሮ በአንዲት ቤት አምስት ሰዎች ይኖራሉና፤ ሦስቱም በሁለቱ ላይ ሁለቱም በሦስቱ ላይ ተነሥተው ይለያያሉ።
53Tėvas stos prieš sūnų, o sūnus prieš tėvą, motina prieš dukterį, o duktė prieš motiną; anyta prieš marčią, ir marti prieš anytą”.
53አባት በልጁ ላይ ልጅም በአባቱ ላይ፥ እናት በልጅዋ ላይ ልጅዋም በእናትዋ ላይ፥ አማት በምራትዋ ላይ ምራትም በአማትዋ ላይ ተነሥተው ይለያያሉ።
54Jėzus pasakė ir minioms: “Matydami debesį, kylantį vakaruose, tuoj pat sakote: ‘Ateina lietus’, ir taip atsitinka.
54ደግሞም ሕዝቡን እንዲህ አለ። ደመና ከምዕራብ ሲወጣ ባያችሁ ጊዜ፥ ወዲያው። ዝናብ ይመጣል ትላላችሁ፥ እንዲሁም ይሆናል፤
55Pučiant pietų vėjui, tvirtinate: ‘Bus karšta’, ir taip būna.
55በአዜብም ነፋስ ሲነፍስ። ትኩሳት ይሆናል ትላላችሁ፥ ይሆንማል።
56Veidmainiai! Jūs mokate atpažinti žemės ir dangaus veidą, tai kodėl gi neatpažįstate šio laiko?
56እናንት ግብዞች፥ የምድሩንና የሰማዩን ፊት ልትመረምሩ ታውቃላችሁ፥ ነገር ግን ይህን ዘመን የማትመረምሩ እንዴት ነው?
57Kodėl patys nenusprendžiate, kas teisu?
57ራሳችሁ ደግሞ ጽድቅን የማትፈርዱ ስለ ምን ነው?
58Kai eini su kaltintoju pas valdininką, pasistenk dar kelyje su juo susitarti, kad jis tavęs nenusitemptų pas teisėją, teisėjas neatiduotų teismo vykdytojui, o teismo vykdytojas neįmestų tavęs į kalėjimą.
58ከባላጋራህ ጋር ወደ ሹም ብትሄድ፥ ወደ ዳኛ እንዳይጐትትህ ዳኛውም ለሎሌው አሳልፎ እንዳይሰጥህ ሎሌውም በወኅኒ እንዳይጥልህ፥ ገና በመንገድ ሳለህ ከባላጋራህ እንድትታረቅ ትጋ።
59Sakau tau: iš ten neišeisi, kol neatsiteisi ligi paskutinio skatiko”.
59እልሃለሁ፥ የመጨረሻዋን ግማሽ ሳንቲም እስክትከፍል ድረስ ከዚያ ከቶ አትወጣም።