Lithuanian

Amharic: New Testament

Luke

13

1Tuo pačiu metu atėjo keli žmonės ir papasakojo Jam apie galilėjiečius, kurių kraują Pilotas sumaišė su jų aukomis.
1በዚያን ጊዜም ሰዎች መጥተው ጲላጦስ ደማቸውን ከመሥዋዕታቸው ጋር ስላደባለቀው ስለ ገሊላ ሰዎች አወሩለት።
2Jėzus, atsakydamas jiems, tarė: “Ar manote, kad tie galilėjiečiai buvo didesni nusidėjėliai už visus kitus galilėjiečius ir todėl taip nukentėjo?
2ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። እነዚህ የገሊላ ሰዎች ይህ ስለ ደረሰባቸው ከገሊላ ሰዎች ሁሉ ይልቅ ኃጢአተኞች የሆኑ ይመስሉአችኋልን?
3Ne, sakau jums! Bet jei neatgailausite, visi taip pat pražūsite.
3እላችኋለሁ፥ አይደለም፤ ነገር ግን ንስሐ ባትገቡ ሁላችሁ እንዲሁ ትጠፋላችሁ።
4Arba anie aštuoniolika, kuriuos užgriuvo bokštas prie Siloamo ir užmušė; jūs manote, kad jie buvo kaltesni už visus kitus Jeruzalės gyventojus?
4ወይስ በሰሌሆም ግንቡ የወደቀባቸውና የገደላቸው እነዚያ አሥራ ስምንት ሰዎች በኢየሩሳሌም ከሚኖሩት ሁሉ ይልቅ በደለኞች ይመስሉአችኋልን? አይደለም፥ እላችኋለሁ፤
5Ne, sakau jums, bet jei neatgailausite, visi taip pat pražūsite”.
5ነገር ግን ንስሐ ባትገቡ ሁላችሁ እንደዚሁ ትጠፋላችሁ።
6Jis pasakė palyginimą: “Žmogus turėjo savo vynuogyne pasisodinęs figmedį. Kartą jis atėjo pažiūrėti jo vaisių, bet nerado.
6ይህንም ምሳሌ አለ። ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው፥ ፍሬም ሊፈልግባት መጥቶ ምንም አላገኘም።
7Ir tarė sodininkui: ‘Jau treji metai, kai ateinu ieškoti šio figmedžio vaisių ir vis nerandu. Nukirsk jį, kam dar žemę alina!’
7የወይን አትክልት ሠራተኛውንም። እነሆ፥ ከዚህች በለስ ፍሬ ልፈልግ ሦስት ዓመት እየመጣሁ ምንም አላገኘሁም፤ ቍረጣት፤ ስለ ምን ደግሞ መሬቱን ታጐሳቍላለች? አለው።
8Anas jam atsakė: ‘Šeimininke, palik dar jį šiais metais. Aš jį apkasiu ir patręšiu.
8እርሱ ግን መልሶ። ጌታ ሆይ፥ ዙሪያዋን እስክኰተኵትላትና ፋንድያ እስካፈስላት ድረስ በዚች ዓመት ደግሞ ተዋት።
9Jei jis duos vaisių, gerai. O jei ne, tai iškirsk jį!’ ”
9ወደ ፊትም ብታፈራ፥ ደኅና ነው፤ ያለዚያ ግን ትቈርጣታለህ አለው።
10Sabato dieną Jėzus mokė vienoje sinagogoje.
10በሰንበትም በአንድ ምኵራብ ያስተምር ነበር።
11Čia buvo moteris, aštuoniolika metų turinti ligos dvasią. Ji buvo sutraukta ir visiškai negalėjo išsitiesti.
11እነሆም፥ ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ የድካም መንፈስ ያደረባት ሴት ነበረች፥ እርስዋም ጐባጣ ነበረች ቀንታም ልትቆም ከቶ አልተቻላትም።
12Jėzus, pamatęs ją, pasišaukė ir tarė: “Moterie, esi išvaduota iš savo ligos!”
12ኢየሱስም ባያት ጊዜ ጠራትና። አንቺ ሴት፥ ከድካምሽ ተፈትተሻል አላት፥ እጁንም ጫነባት፤
13Jis uždėjo ant jos rankas, toji bematant atsitiesė ir ėmė garbinti Dievą.
13ያን ጊዜም ቀጥ አለች፥ እግዚአብሔርንም አመሰገነች።
14Tada sinagogos vyresnysis, supykęs, kad Jėzus išgydė ją sabato dieną, pasakė miniai: “Dirbamos yra šešios dienos. Ateikite jomis ir gydykitės, o ne per sabatą!”
14የምኵራብ አለቃ ግን ኢየሱስ በሰንበት ስለ ፈወሰ ተቈጥቶ መለሰና ሕዝቡን። ሊሠራባቸው የሚገባ ስድስት ቀኖች አሉ፤ እንግዲህ በእነርሱ መጥታችሁ ተፈወሱ እንጂ በሰንበት አይደለም አለ።
15Viešpats jam atsakė: “Veidmainy! Argi kas iš jūsų neatriša per sabatą nuo ėdžių savo jaučio ar asilo ir nenuveda pagirdyti?
15ጌታም መልሶ። እናንተ ግብዞች፥ ከእናንተ እያንዳንዱ በሰንበት በሬውን ወይስ አህያውን ከግርግሙ ፈትቶ ውኃ ሊያጠጣው ይወስደው የለምን?
16Argi šios Abraomo dukters, kurią šėtonas laikė surišęs jau aštuoniolika metų, nereikėjo išvaduoti iš pančių sabato dieną?”
16ይህችም የአብርሃም ልጅ ሆና ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ ሰይጣን ያሰራት በሰንበት ቀን ከዚህ እስራት ልትፈታ አይገባምን? አለው።
17Kai Jis tai kalbėjo, visi Jo priešininkai liko sugėdinti, o minia džiaugėsi visais šlovingais Jo atliktais darbais.
17ይህንም ሲናገር ሳለ የተቃወሙት ሁሉ አፈሩ፤ ከእርሱም በተደረገው ድንቅ ሁሉ ሕዝቡ ሁሉ ደስ አላቸው።
18Jis tarė: “Į ką panaši Dievo karalystė, ir su kuo ją palyginsiu?
18እርሱም። የእግዚአብሔር መንግሥት ምን ትመስላለች፥ በምንስ አስመስላታለሁ?
19Ji panaši į garstyčios grūdą, kurį ėmė žmogus ir pasėjo savo darže. Ji išaugo į aukštą medelį ir padangių paukščiai susisuko lizdus jo šakose”.
19ሰው ወስዶ በአትክልቱ የጣላትን የሰናፍጭ ቅንጣት ትመስላለች፤ አደገችም ታላቅ ዛፍም ሆነች፥ የሰማይ ወፎችም በቅርንጫፎችዋ ሰፈሩ አለ።
20Jis vėl tarė: “Su kuo palyginsiu Dievo karalystę?
20ደግሞም፥ የእግዚአብሔርን መንግሥት በምን አስመስላታለሁ?
21Ji panaši į raugą, kurį ėmusi moteris įmaišė į tris saikus miltų, ir nuo jo viskas įrūgo”.
21ሴት ወስዳ ሁሉ እስኪቦካ ድረስ በሦስት መስፈሪያ ዱቄት የሸሸገችውን እርሾ ትመስላለች አለ።
22Jėzus ėjo mokydamas per miestelius bei kaimus ir keliavo į Jeruzalę.
22ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ ከተማዎችንና መንደሮችን እያስተማረ ያልፍ ነበር።
23Kažkas paklausė Jį: “Viešpatie, ar maža bus išgelbėtųjų?” Jis atsakė jiems:
23አንድ ሰውም። ጌታ ሆይ፥ የሚድኑ ጥቂቶች ናቸውን? አለው። እርሱም እንዲህ አላቸው።
24“Stenkitės įeiti pro siaurus vartus. Sakau jums, daugelis bandys įeiti, bet neįstengs.
24በጠበበው በር ለመግባት ተጋደሉ፤ እላችኋለሁና፥ ብዙዎች ሊገቡ ይፈልጋሉ አይችሉምም።
25Kai namų Šeimininkas atsikels ir užrakins duris, jūs, stovėdami lauke, pradėsite belsti į duris ir prašyti: ‘Viešpatie, Viešpatie, atidaryk mums!’ O Jis atsakys: ‘Aš nežinau, iš kur jūs’.
25ባለቤቱ ተነሥቶ በሩን ከቈለፈ በኋላ፥ እናንተ በውጭ ቆማችሁ። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ ክፈትልን እያላችሁ በሩን ልታንኳኩ ትጀምራላችሁ እርሱም መልሶ። ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም ይላችኋል።
26Tada imsite sakyti: ‘Mes valgėme ir gėrėme Tavo akivaizdoje, Tu mokei mūsų gatvėse’.
26በዚያን ጊዜም። በፊትህ በላን ጠጣንም በአደባባያችንም አስተማርህ ልትሉ ትጀምራላችሁ፤
27O Jis tars: ‘Sakau jums, Aš nežinau, iš kur jūs. Eikite šalin nuo manęs, visi piktadariai!’
27እርሱም። እላችኋለሁ፥ ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም፤ ሁላችሁ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ይላችኋል።
28Ten bus verksmo ir dantų griežimo, kai pamatysite Abraomą, Izaoką, Jokūbą ir visus pranašus Dievo karalystėje, o patys būsite išmesti laukan.
28አብርሃምንና ይስሐቅን ያዕቆብንም ነቢያትንም ሁሉ በእግዚአብሔር መንግሥት ባያችሁ ጊዜ፥ እናንተ ግን ወደ ውጭ ተጥላችሁ ስትቀሩ፥ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።
29Ir ateis iš rytų ir vakarų, iš šiaurės ir pietų ir sėsis prie stalo Dievo karalystėje.
29ከምሥራቅና ከምዕራብም ከሰሜንና ከደቡብም ይመጣሉ፥ በእግዚአብሔርም መንግሥት በማዕድ ይቀመጣሉ።
30Ir štai yra paskutinių, kurie bus pirmi, ir pirmų, kurie bus paskutiniai”.
30እነሆም፥ ከኋለኞች ፊተኞች የሚሆኑ አሉ፥ ከፊተኞችም ኋለኞች የሚሆኑ አሉ።
31Tą pačią dieną atėjo keli fariziejai ir pasakė Jėzui: “Eik iš čia, pasišalink, nes Erodas nori Tave nužudyti”.
31በዚያን ሰዓት ከፈሪሳውያን አንዳንዱ ቀርበው። ሄሮድስ ሊገድልህ ይወዳልና ከዚህ ውጣና ሂድ አሉት።
32Jis jiems atsakė: “Eikite ir pasakykite tam lapei: ‘Štai Aš išvarinėju demonus ir gydau šiandien, tai darysiu ir rytoj, o trečią dieną būsiu viską atlikęs.
32እንዲህም አላቸው። ሄዳችሁ ለዚያች ቀበሮ። እነሆ፥ ዛሬና ነገ አጋንንትን አወጣለሁ በሽተኞችንም እፈውሳለሁ፥ በሦስተኛውም ቀን እፈጸማለሁ በሉአት።
33Bet šiandien ir rytoj, ir poryt turiu keliauti, nes negali taip būti, kad pranašas žūtų ne Jeruzalėje’ ”.
33ዳሩ ግን ነቢይ ከኢየሩሳሌም ውጭ ይጠፋ ዘንድ አይገባውምና ዛሬና ነገ ከነገ በስቲያም ልሄድ ያስፈልገኛል።
34“Jeruzale, Jeruzale! Tu žudai pranašus ir užmėtai akmenimis tuos, kurie pas tave siųsti. Kiek kartų norėjau surinkti tavo vaikus kaip višta savo viščiukus po sparnais, o tu nenorėjai!
34ኢየሩሳሌም፥ ኢየሩሳሌም፥ ነቢያትን የምትገድል ወደ እርስዋ የተላኩትንም የምትወግር፥ ዶሮ ጫጩቶችዋን በክንፎችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ፥ እናንተም አልወደዳችሁም።
35Štai jūsų namai paliekami jums tušti. Iš tiesų sakau jums: jūs manęs nebematysite, kol ateis laikas, kada tarsite: ‘Palaimintas Tas, kuris ateina Viešpaties vardu!’ ”
35እነሆ፥ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል። እላችኋለሁም፥ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እስክትሉ ድረስ ከእንግዲህ ወዲህ አታዩኝም።