1Kartą sabato dieną Jėzus atėjo į vieno fariziejų vyresniojo namus valgyti, o jie atidžiai stebėjo Jį.
1በሰንበትም ከፈሪሳውያን አለቆች ወደ አንዱ ቤት እንጀራ ሊበላ በገባ ጊዜ እነርሱ ይጠባበቁት ነበር።
2Ir štai Jį pasitiko vandenlige sergantis žmogus.
2እነሆም፥ ሆዱ የተነፋ ሰው በፊቱ ነበረ።
3Jėzus kreipėsi į Įstatymo mokytojus ir fariziejus: “Leistina per sabatą gydyti ar ne?”
3ኢየሱስም መልሶ። በሰንበት መፈወስ ተፈቅዶአልን ወይስ አልተፈቀደም? ብሎ ለሕግ አዋቂዎችና ለፈሪሳውያን ተናገረ።
4Tie tylėjo. Tada Jis ėmė, išgydė jį ir paleido.
4እነርሱ ግን ዝም አሉ። ይዞም ፈወሰውና አሰናበተው።
5O jiems pasakė: “Jei kurio iš jūsų asilas ar jautis įkristų į šulinį, argi tučtuojau neištrauktų jo per sabatą?”
5ከእናንተ አህያው ወይስ በሬው በጕድጓድ ቢወድቅ በሰንበት ወዲያው የማያወጣው ማን ነው? አላቸው።
6Ir jie nesugebėjo Jam į tai atsakyti.
6ስለዚህ ነገርም ሊመልሱለት አልተቻላቸውም።
7Matydamas, kaip svečiai rinkosi pirmąsias vietas prie stalo, Jis pasakė jiems palyginimą:
7የታደሙትንም የከበሬታ ስፍራ እንደ መረጡ ተመልክቶ ምሳሌ ነገራቸው እንዲህ ሲል።
8“Kai kas nors tave pakvies į vestuves, nesėsk pirmoje vietoje, kad kartais nebūtų pakviesta garbingesnio už tave,
8ማንም ለሰርግ ቢጠራህ በከበሬታ ስፍራ አትቀመጥ፤ ምናልባት ከአንተ ይልቅ የከበረ ተጠርቶ ይሆናልና አንተን እርሱንም የጠራ መጥቶ።
9ir atėjęs tas, kuris tave ir jį pakvietė, netartų tau: ‘Užleisk jam vietą!’ Tada sugėdintas turėsi sėstis į paskutinę vietą.
9ለዚህ ስፍራ ተውለት ይልሃል፥ በዚያን ጊዜም እያፈርህ በዝቅተኛው ስፍራ ልትሆን ትጀምራለህ።
10Kai būsi pakviestas, eik ir sėskis paskutinėje vietoje, kad tas, kuris tave pakvietė, atėjęs galėtų pasakyti: ‘Bičiuli, persėsk aukščiau!’ Tada tau bus garbė visų prie stalo sėdinčiųjų akivaizdoje.
10ነገር ግን በተጠራህ ጊዜ፥ የጠራህ መጥቶ። ወዳጄ ሆይ፥ ወደ ላይ ውጣ እንዲልህ፥ ሄደህ በዝቅተኛው ስፍራ ተቀመጥ፤ ያን ጊዜም ከአንተ ጋር በተቀመጡት ሁሉ ፊት ክብር ይሆንልሃል።
11Kiekvienas, kuris save aukština, bus pažemintas, o kuris save žemina, bus išaukštintas”.
11ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱንም የሚያዋርድ ከፍ ይላል።
12Pakvietusiam Jį vaišių Jėzus irgi pasakė: “Keldamas pietus ar vakarienę, nekviesk nei savo draugų, nei brolių, nei giminaičių, nei turtingų kaimynų, kad kartais jie savo ruožtu nepakviestų tavęs ir tau nebūtų atlyginta.
12የጠራውንም ደግሞ እንዲህ አለው። ምሳ ወይም እራት ባደረግህ ጊዜ፥ እነርሱ ደግሞ በተራቸው ምናልባት እንዳይጠሩህ ብድራትም እንዳይመልሱልህ፥ ወዳጆችህንና ወንድሞችህን ዘመዶችህንም ባለ ጠጎች ጎረቤቶችህንም አትጥራ።
13Rengdamas vaišes, geriau pasikviesk vargšų, paliegėlių, luošų ir aklų,
13ነገር ግን ግብዣ ባደረግህ ጊዜ ድሆችንና ጕንድሾችን አንካሶችንም ዕውሮችንም ጥራ፤
14tai būsi palaimintas, nes jie neturi kuo atsilyginti. Tuomet tau bus atlyginta teisiųjų prisikėlime”.
14የሚመልሱት ብድራት የላቸውምና ብፁዕ ትሆናለህ፤ በጻድቃን ትንሣኤ ይመለስልሃልና።
15Tai išgirdęs, vienas iš sėdinčiųjų prie stalo tarė Jam: “Palaimintas, kas valgys duoną Dievo karalystėje!”
15ከተቀመጡትም አንዱ ይህን ሰምቶ። በእግዚአብሔር መንግሥት እንጀራ የሚበላ ብፁዕ ነው አለው።
16Tada Jėzus jam pasakė: “Vienas žmogus iškėlė didelę puotą ir pakvietė daug svečių.
16እርሱ ግን እንዲህ አለው። አንድ ሰው ታላቅ እራት አድርጎ ብዙዎችን ጠራ፤
17Atėjus puotos metui, jis pasiuntė tarną pranešti pakviestiesiems: ‘Ateikite, jau viskas surengta’.
17በእራትም ሰዓት የታደሙትን። አሁን ተዘጋጅቶአልና ኑ እንዲላቸው ባሪያውን ላከ።
18Tada jie visi kaip vienas pradėjo atsiprašinėti. Vienas jam tarė: ‘Nusipirkau dirvą ir būtinai turiu eiti jos apžiūrėti. Prašau mane pateisinti’.
18ሁላቸውም በአንድነት ያመካኙ ጀመር። የፊተኛው። መሬት ገዝቼአለሁ ወጥቼም ላየው በግድ ያስፈልገኛል፤ ይቅር እንድትለኝ እለምንሃለሁ አለው።
19Kitas sakė: ‘Pirkau penkis jungus jaučių ir einu jų išmėginti. Prašau mane pateisinti’.
19ሌላውም። አምስት ጥምድ በሬዎች ገዝቼአለሁ ልፈትናቸውም እሄዳለሁ፤ ይቅር እንድትለኝ እለምንሃለሁ አለው።
20Trečias tarė: ‘Vedžiau žmoną, todėl negaliu ateiti’.
20ሌላውም። ሚስት አግብቼአለሁ ስለዚህም ልመጣ አልችልም አለው።
21Tarnas sugrįžęs viską papasakojo šeimininkui. Šis supyko ir įsakė tarnui: ‘Skubiai eik į miesto gatves ir skersgatvius ir vesk čia vargšus, paliegėlius, luošus ir aklus’.
21ባሪያውም ደርሶ ይህን ለጌታው ነገረው። በዚያን ጊዜ ባለቤቱ ተቆጥቶ ባሪያውን። ወደ ከተማ ጎዳናና ወደ ስላች ፈጥነህ ውጣ ድሆችንና ጕንድሾችን አንካሶችንና ዕውሮችንም ወደዚህ አግባ አለው።
22Tarnas vėl pranešė: ‘Šeimininke, kaip liepei,padaryta, bet dar yra vietos’.
22ባሪያውም። ጌታ ሆይ፥ እንዳዘዝኸኝ ተደርጎአል፥ ገናም ስፍራ አለ አለው።
23Tada šeimininkas tarė tarnui: ‘Eik į kelius bei patvorius ir priversk ateiti, kad mano namai būtų pilni.
23ጌታውም ባሪያውን። ቤቴ እንዲሞላ ወደ መንገድና ወደ ቅጥር ውጣና ይገቡ ዘንድ ግድ በላቸው፤
24Sakau jums,nė vienas iš anų pakviestųjų žmonių neragaus mano vaišių’ ”.
24እላችኋለሁና፥ ከታደሙት ከእነዚያ ሰዎች አንድ ስንኳ እራቴን አይቀምስም አለው።
25Kartu su Juo ėjo didelės minios. Atsigręžęs Jis tarė žmonėms:
25ብዙም ሕዝብ ከእርሱ ጋር ይሄዱ ነበር፥ ዘወር ብሎም እንዲህ አላቸው።
26“Jei kas ateina pas mane ir nelaiko neapykantoje savo tėvo, motinos, žmonos, vaikų, brolių, seserų ir net savo gyvybės,negali būti mano mokinys.
26ማንም ወደ እኔ የሚመጣ ቢኖር አባቱንና እናቱን ሚስቱንም ልጆቹንም ወንድሞቹንም እኅቶቹንም የራሱን ሕይወት ስንኳ ሳይቀር ባይጠላ፥ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም።
27Kas neneša savo kryžiaus ir neseka manimi, negali būti mano mokinys.
27ማንም መስቀሉን ተሸክሞ በኋላዬ የማይመጣ፥ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም።
28Kas iš jūsų, norėdamas pastatyti bokštą, pirmiau atsisėdęs neskaičiuoja išlaidų, kad žinotų, ar turės iš ko užbaigti?
28ከእናንተ ግንብ ሊሠራ የሚወድ ለመደምደሚያ የሚበቃ ያለው እንደ ሆነ አስቀድሞ ተቀምጦ ከሳራውን የማይቈጥር ማን ነው?
29Kad kartais, padėjus pamatą ir nebaigus, žmonės matydami nesišaipytų iš jo,
29ያለዚያ መሠረቱን ቢመሠርት፥ ሊደመድመውም ቢያቅተው፥ ያዩት ሁሉ።
30sakydami: ‘Šitas žmogus pradėjo statyti ir neįstengia baigti’.
30ይህ ሰው ሊሠራ ጀምሮ ሊደመድመው አቃተው ብለው ሊዘብቱበት ይጀምራሉ።
31Arba koks karalius, traukdamas į karą prieš kitą karalių, pirmiau atsisėdęs nesvarsto, ar, turėdamas dešimt tūkstančių kareivių, pajėgs stoti į kovą su tuo, kuris ateina prieš jį su dvidešimčia tūkstančių?!
31ወይም ሌላውን ንጉሥ በጦርነት ሊጋጠም የሚሄድ፥ ከሁለት እልፍ ጋር የሚመጣበትን በአንድ እልፍ ሊገናኝ የሚችል እንደ ሆነ አስቀድሞ ተቀምጦ የማያስብ ንጉሥ ማን ነው?
32Jei ne, tai, anam dar toli esant, siunčia pasiuntinius tartis dėl taikos.
32ባይሆንስ ሌላው ገና ሩቅ ሳለ መልክተኞች ልኮ ዕርቅ ይለምናል።
33Taip pat kiekvienas iš jūsų, kuris neatsižada viso, ką turi, negali būti mano mokinys”.
33እንግዲህ እንደዚሁ ማንም ከእናንተ ያለውን ሁሉ የማይተው ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም።
34“Druskageras daiktas. Bet jeigu druska netektų sūrumo, kuo ją reikėtų pasūdyti?
34ጨው መልካም ነው፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፈጣል?
35Ji nebetinka nei dirvai, nei mėšlui; ją išmeta laukan. Kas turi ausis klausytiteklauso!”
35ለምድር ቢሆን ለፍግ መቈለያም ቢሆን አይረባም፤ ወደ ውጭ ይጥሉታል። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።