1Prie Jėzaus artindavosi visi muitininkai ir nusidėjėliai Jo pasiklausyti.
1ቀራጮችና ኃጢአተኞችም ሁሉ ሊሰሙት ወደ እርሱ ይቀርቡ ነበር።
2Fariziejai ir Rašto žinovai murmėjo, sakydami: “Šitas priima nusidėjėlius ir su jais valgo”.
2ፈሪሳውያንና ጻፎችም። ይህስ ኃጢአተኞችን ይቀበላል ከእነርሱም ጋር ይበላል ብለው እርስ በርሳቸው አንጐራጐሩ።
3Tada Jis pasakė jiems palyginimą:
3ይህንም ምሳሌ ነገራቸው እንዲህ ሲል።
4“Kas iš jūsų, turėdamas šimtą avių ir vienai nuklydus, nepalieka dykumoje devyniasdešimt devynių ir neieško pražuvusios, kol suranda?
4መቶ በግ ያለው ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ፥ ዘጠና ዘጠኙን በበረሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሄድ ከእናንተ ማን ነው?
5Radęs su džiaugsmu dedasi ją ant pečių
5ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል፤
6ir, sugrįžęs namo, susikviečia draugus bei kaimynus, sakydamas: ‘Džiaukitės drauge su manimi, radau savo avį, kuri buvo pražuvusi!’
6ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ። የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ ይላቸዋል።
7Sakau jums, taip ir danguje bus daugiau džiaugsmo dėl vieno atgailaujančio nusidėjėlio negu dėl devyniasdešimt devynių teisiųjų, kuriems nereikia atgailos.
7እላችኋለሁ፥ እንዲሁ ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።
8Arba kuri moteris, turėdama dešimtį drachmų ir vieną pametusi, neužsidega žiburio, nešluoja namų ir rūpestingai neieško, kol suranda?
8ወይም አሥር ድሪም ያላት አንድ ድሪም ቢጠፋባት፥ መብራት አብርታ ቤትዋንም ጠርጋ እስክታገኘው ድረስ አጥብቃ የማትፈልግ ሴት ማን ናት?
9Radusi susivadina drauges bei kaimynes ir sako: ‘Džiaukitės su manimi, nes radau drachmą, kurią buvau pametusi’.
9ባገኘችውም ጊዜ ወዳጆችዋንና ጐረቤቶችዋን በአንድነት ጠርታ። የጠፋውን ድሪሜን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ ትላቸዋለች።
10Sakau jums, šitaip džiaugiasi Dievo angelai dėl vieno atgailaujančio nusidėjėlio”.
10እላችኋለሁ፥ እንዲሁ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል።
11Jis kalbėjo toliau: “Vienas žmogus turėjo du sūnus.
11እንዲህም አለ። አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት።
12Kartą jaunesnysis tarė tėvui: ‘Tėve, atiduok man priklausančią palikimo dalį’. Tėvas padalijo sūnums turtą.
12ከእነርሱም ታናሹ አባቱን። አባቴ ሆይ፥ ከገንዘብህ የሚደርሰኝን ክፍል ስጠኝ አለው። ገንዘቡንም አካፈላቸው።
13Praėjus kelioms dienoms, jaunesnysis sūnus, pasiėmęs savo dalį, iškeliavo į tolimą šalį. Ten, palaidai gyvendamas, iššvaistė savo turtą.
13ከጥቂት ቀንም በኋላ ታናሹ ልጅ ገንዘቡን ሁሉ ሰብስቦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ፥ ከዚያም እያባከነ ገዘቡን በተነ።
14Kai viską išleido, toje šalyje kilo didelis badas, ir jis pradėjo stokoti.
14ሁሉንም ከከሰረ በኋላ በዚያች አገር ጽኑ ራብ ሆነ፥ እርሱም ይጨነቅ ጀመር።
15Tada apsistojo pas vieną tos šalies gyventoją. Tas jį pasiuntė į laukus kiaulių ganyti.
15ሄዶም ከዚያች አገር ሰዎች ከአንዱ ጋር ተዳበለ፥ እርሱም እሪያ ሊያሰማራ ወደ ሜዳ ሰደደው።
16Jis geidė prikimšti pilvą bent ankštimis, kurias ėdė kiaulės, bet ir tų niekas jam neduodavo.
16እሪያዎችም ከሚበሉት አሰር ሊጠግብ ይመኝ ነበር፥ የሚሰጠውም አልነበረም።
17Tada susiprotėjęs jis tarė: ‘Kiek mano tėvo samdinių apsčiai turi duonos, o aš čia mirštu iš bado!
17ወደ ልቡም ተመልሶ እንዲህ አለ። እንጀራ የሚተርፋቸው የአባቴ ሞያተኞች ስንት ናቸው? እኔ ግን ከዚህ በራብ እጠፋለሁ።
18Kelsiuos, eisiu pas tėvą ir sakysiu: ‘Tėve, nusidėjau dangui ir tau.
18ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና። አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥
19Nesu vertas vadintis tavo sūnumi. Priimk mane bent samdiniu!’
19ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም፤ ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ እለዋለሁ።
20Jis pakilo ir iškeliavo pas tėvą. Jam dar toli esant, tėvas jį pamatė ir, apimtas gailesčio, pribėgo, puolė ant kaklo ir meiliai pabučiavo.
20ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ። እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት፥ ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው።
21O sūnus jam tarė: ‘Tėve, nusidėjau dangui ir tau, nebesu vertas vadintis tavo sūnumi’.
21ልጁም። አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም አለው።
22Bet tėvas įsakė savo tarnams: ‘Kuo greičiau atneškite geriausią drabužį ir apvilkite jį. Užmaukite jam ant piršto žiedą, apaukite kojas!
22አባቱ ግን ባሪያዎቹን አለ። ፈጥናችሁ ከሁሉ የተሻለ ልብስ አምጡና አልብሱት፥ ለእጁ ቀለበት ለእግሩም ጫማ ስጡ፤
23Atveskite nupenėtą veršį ir papjaukite! Valgysim ir linksminsimės!
23የሰባውን ፊሪዳ አምጥታችሁ እረዱት፥ እንብላም ደስም ይበለን፤
24Nes šis mano sūnus buvo miręs ir vėl atgijo, buvo pražuvęs ir atsirado’. Ir jie pradėjo linksmintis.
24ይህ ልጄ ሞቶ ነበርና ደግሞም ሕያው ሆኖአል፤ ጠፍቶም ነበር ተገኝቶአልም። ደስም ይላቸው ጀመር።
25O vyresnysis jo sūnus buvo laukuose. Kai grįždamas prisiartino prie namų, išgirdo muziką ir šokius.
25ታላቁ ልጁ በእርሻ ነበረ፤ መጥቶም ወደ ቤት በቀረበ ጊዜ የመሰንቆና የዘፈን ድምፅ ሰማ፤
26Pasišaukęs vieną iš tarnų, jis paklausė, kas čia dedasi.
26ከብላቴናዎችም አንዱን ጠርቶ። ይህ ምንድር ነው? ብሎ ጠየቀ።
27Tas jam atsakė: ‘Sugrįžo tavo brolis, tai tėvas papjovė nupenėtą veršį, nes sulaukė jo sveiko’.
27እርሱም። ወንድምህ መጥቶአልና በደኅና ስላገኘው አባትህ የሰባውን ፊሪዳ አረደለት አለው።
28Tada šis supyko ir nenorėjo eiti vidun. Tėvas išėjęs ėmė jį kviesti.
28ተቈጣም ሊገባም አልወደደም፤ አባቱም ወጥቶ ለመነው።
29O jis atsakė tėvui: ‘Štai jau tiek metų tau tarnauju ir niekad tavo įsakymo neperžengiau, o tu man nė karto nedavei nė ožiuko pasilinksminti su draugais.
29እርሱ ግን መልሶ አባቱን። እነሆ፥ ይህን ያህል ዓመት እንደ ባሪያ ተገዝቼልሃለሁ ከትእዛዝህም ከቶ አልተላለፍሁም፤ ለእኔም ከወዳጆቼ ጋር ደስ እንዲለኝ አንድ ጥቦት ስንኳ አልሰጠኸኝም፤
30Bet vos tik sugrįžo šitas tavo sūnus, prarijęs tavo turtą su kekšėmis, tu tuojau papjovei jam nupenėtą veršį’.
30ነገር ግን ገንዘብህን ከጋለሞቶች ጋር በልቶ ይህ ልጅህ በመጣ ጊዜ፥ የሰባውን ፊሪዳ አረድህለት አለው።
31Tėvas atsakė: ‘Sūnau, tu visuomet su manimi, ir visa, kas mano, yra ir tavo.
31እርሱ ግን። ልጄ ሆይ፥ አንተ ሁልጊዜ ከእኔ ጋር ነህ፥ ለእኔም የሆነ ሁሉ የአንተ ነው፤
32Bet reikėjo džiaugtis ir linksmintis, nes tavo brolis buvo miręs ir vėl atgijo, buvo pražuvęs ir atsirado!’ ”
32ዳሩ ግን ይህ ወንድምህ ሞቶ ነበረ ሕያው ስለ ሆነ ጠፍቶም ነበር ስለ ተገኘ ደስ እንዲለን ፍሥሐም እንድናደርግ ይገባናል አለው።