1Jėzus kalbėjo ir savo mokiniams: “Buvo vienas turtingas žmogus ir turėjo ūkvedį. Tas buvo jam apskųstas, esą eikvojąs jo turtą.
1ደግሞም ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አለ። መጋቢ የነበረው አንድ ባለ ጠጋ ሰው ነበረ፥ በእርሱ ዘንድ። ይህ ሰው ያለህን ይበትናል ብለው ከሰሱት።
2Tuomet, pasišaukęs jį, šeimininkas pasakė: ‘Ką aš girdžiu apie tave šnekant? Duok savo ūkvedžiavimo apyskaitą, nes daugiau nebegalėsi būti ūkvedžiu’.
2ጠርቶም። ይህ የምሰማብህ ምንድር ነው? ወደ ፊት ለእኔ መጋቢ ልትሆን አትችልምና የመጋቢነትህን ሂሳብ አስረክበኝ አለው።
3O ūkvedys tarė sau: ‘Ką veiksiu, kad šeimininkas atima iš manęs ūkvedžiavimą? Kasti neįstengiu, o elgetautigėda.
3መጋቢውም በልቡ። ጌታዬ መጋቢነቱን ከእኔ ይወስዳልና ምን ላድርግ? ለመቈፈር ኃይል የለኝም፥ መለመንም አፍራለሁ።
4Žinau, ką daryti, kad žmonės mane priimtų į savo namus, kai būsiu atleistas iš tarnybos’.
4ከመጋቢነቱ ብሻር በቤታቸው እንዲቀበሉኝ የማደርገውን አውቃለሁ አለ።
5Jis pasikvietė po vieną savo šeimininko skolininkus ir klausė pirmąjį: ‘Kiek esi skolingas mano šeimininkui?’
5የጌታውንም ባለ ዕዳዎች እያንዳንዳቸውን ጠርቶ የፊተኛውን። ለጌታዬ ምን ያህል ዕዳ አለብህ? አለው።
6Šis atsakė: ‘Šimtą statinių aliejaus’. Tada jis tarė: ‘Imk savo skolos raštą, sėsk ir tuoj pat rašyk: penkiasdešimt’.
6እርሱም። መቶ ማድጋ ዘይት አለ። ደብዳቤህን እንካ ፈጥነህም ተቀምጠህ አምሳ ብለህ ጻፍ አለው።
7Paskui klausė kitą: ‘O kiek tu skolingas?’ Anas atsakė: ‘Šimtą saikų kviečių’. Jis tarė: ‘Imk skolos raštą ir rašyk: aštuoniasdešimt’.
7በኋላም ሌላውን። አንተስ ስንት ዕዳ አለብህ? አለው። እርሱም። መቶ ጫን ስንዴ አለ። ደብዳቤህን እንካ ሰማንያ ብለህም ጻፍ አለው።
8Šeimininkas pagyrė neteisųjį ūkvedį, kad jis gudriai pasielgė. Šio pasaulio vaikai sumanesni tarp savųjų negu šviesos vaikai”.
8ጌታውም ዓመፀኛውን መጋቢ በልባምነት ስላደረገ አመሰገነው የዚህ ዓለም ልጆች ለትውልዳቸው ከብርሃን ልጆች ይልቅ ልባሞች ናቸውና።
9“Ir Aš jums sakau: darykitės bičiulių neteisiosios Mamonos dėka, kad, jūsų galui atėjus, jie priimtų jus į amžinuosius namus.
9እኔም እላችኋለሁ፥ የዓመፃ ገንዘብ ሲያልቅ በዘላለም ቤቶች እንዲቀበሉአችሁ፥ በእርሱ ወዳጆችን ለራሳችሁ አድርጉ።
10Kas ištikimas mažame dalyke, tas ištikimas ir dideliame, o kas neteisingas mažame, tas neteisingas ir dideliame.
10ከሁሉ በሚያንስ የታመነ በብዙ ደግሞ የታመነ ነው፥ ከሁሉ በሚያንስም የሚያምፅ በብዙ ደግሞ ዓመፀኛ ነው።
11Jei nebuvote ištikimi, tvarkydami neteisiąją Mamoną, tai kas jums patikės tikruosius turtus?
11እንግዲያስ በዓመፃ ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ እውነተኛውን ገንዘብ ማን አደራ ይሰጣችኋል?
12Ir jeigu nebuvote ištikimi su svetimu daiktu, tai kas jums duos tai, kas jūsų?
12በሌላ ሰው ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ የእናንተን ማን ይሰጣችኋል?
13Joks tarnas negali tarnauti dviem šeimininkams, nes jis arba vieno nekęs, o kitą mylės, arba prie vieno prisiriš, o kitą nieku vers. Negalite tarnauti Dievui ir Mamonai”.
13ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ባርያ ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላልና ሁለተኛውንም ይወዳል፥ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል። ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም።
14Visa tai girdėjo mėgstantys pinigus fariziejai ir šaipėsi iš Jėzaus.
14ገንዘብንም የሚወዱ ፈሪሳውያን ይህን ሁሉ ሰምተው ያፌዙበት ነበር።
15O Jis jiems pasakė: “Jūs žmonių akyse dedatės teisūs, bet Dievas mato jūsų širdis. Nes tai, kas žmonėse aukštinama, Dievo akyse bjauru”.
15እንዲህም አላቸው። ራሳችሁን በሰው ፊት የምታጸድቁ እናንተ ናችሁ፥ ነገር ግን እግዚአብሔር ልባችሁን ያውቃል፤ በሰው ዘንድ የከበረ በእግዚአብሔር ፊት ርኵሰት ነውና።
16“Įstatymas ir pranašaiiki Jono; nuo tada skelbiama Dievo karalystė, ir kiekvienas į ją veržiasi.
16ሕግና ነቢያት እስከ ዮሐንስ ነበሩ፤ ከዚያ ጀምሮ የእግዚአብሔር መንግሥት ይሰበካል፤ ሁሉም ወደ እርስዋ በኃይል ይገቡባታል።
17Greičiau dangus ir žemė praeis, negu iš Įstatymo iškris bent vienas brūkšnelis.
17ነገር ግን ከሕግ አንዲት ነጥብ ከምትወድቅ ሰማይና ምድር ሊያልፍ ይቀላል።
18Kiekvienas, kuris atleidžia žmoną ir veda kitąsvetimauja. Ir kas veda vyro atleistąją, taip pat svetimauja”.
18ሚስቱንም የሚፈታ ሁሉ ሌላይቱንም የሚያገባ ያመነዝራል፥ ከባልዋም የተፈታችውን የሚያገባ ያመነዝራል።
19“Gyveno vienas turtuolis. Jis vilkėjo purpuru bei ploniausia drobe ir kasdien ištaigingai linksminosi.
19ቀይ ልብስና ቀጭን የተልባ እግር የለበሰ አንድ ባለ ጠጋ ሰው ነበረ፥ ዕለት ዕለትም እየተመቸው በደስታ ይኖር ነበር።
20O prie jo vartų gulėjo votimis aptekęs elgeta, vardu Lozorius.
20አልዓዛርም የሚባል አንድ ድሀ በቍስል ተወርሶ በደጁ ተኝቶ ነበር፥
21Jis troško numarinti alkį bent trupiniais nuo turtuolio stalo, bet tik šunys atbėgę laižydavo jo votis.
21ከባለ ጠጋውም ማዕድ ከሚወድቀው ፍርፋሪ ሊጠግብ ይመኝ ነበር፤ ውሾች እንኳ መጥተው ቍስሎቹን ይልሱ ነበር።
22Ir štai elgeta mirė ir buvo angelų nuneštas į Abraomo prieglobstį. Mirė ir turtuolis ir buvo palaidotas.
22ድሀውም ሞተ፥ መላእክትም ወደ አብርሃም እቅፍ ወሰዱት፤ ባለ ጠጋው ደግሞ ሞተና ተቀበረ።
23Kentėdamas pragare, jis pakėlė akis ir iš tolo pamatė Abraomą ir jo prieglobstyje Lozorių.
23በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ አየ አልዓዛርንም በእቅፉ።
24Jis ėmė šaukti: ‘Tėve Abraomai, pasigailėk manęs! Atsiųsk Lozorių, kad, suvilgęs vandenyje piršto galą, atvėsintų man liežuvį, nes baisiai kenčiu šioje liepsnoje’.
24እርሱም እየጮኸ። አብርሃም አባት ሆይ፥ ማረኝ፥ በዚህ ነበልባል እሣቀያለሁና የጣቱን ጫፍ በውኃ ነክሮ መላሴን እንዲያበርድልኝ አልዓዛርን ስደድልኝ አለ።
25Bet Abraomas atsakė: ‘Atsimink, sūnau, kad tu gyvendamas atsiėmei savo gėrybes, o Lozoriustik nelaimes. Todėl jis susilaukė paguodos, o tu kenti.
25አብርሃም ግን። ልጄ ሆይ፥ አንተ በሕይወትህ ሳለህ መልካም እንደ ተቀበልህ አስብ አልዓዛርም እንዲሁ ክፉ፤ አሁን ግን እርሱ በዚህ ይጽናናል አንተም ትሣቀያለህ።
26Be to, mus nuo jūsų skiria milžiniška praraja, ir niekas iš čia panorėjęs negali nueiti pas jus, nei iš ten persikelti pas mus’.
26ከዚህም ሁሉ ጋር ከዚህ ወደ እናንተ ሊያልፉ የሚፈልጉ እንዳይችሉ፥ ወዲያ ያሉ ደግሞ ወደ እኛ እንዳይሻገሩ በእኛና በእናንተ መካከል ታላቅ ገደል ተደርጎአል አለ።
27Tas vėl tarė: ‘Tai meldžiu tave, tėve, nusiųsk jį bent į mano tėvo namus,
27እርሱም። እንኪያስ፥ አባት ሆይ፥ ወደ አባቴ ቤት እንድትሰደው እለምንሃለሁ፤ አምስት ወንድሞች አሉኝና፤
28nes aš turiu penkis brolius. Teįspėja juos, kad ir jie nepatektų į šią kančių vietą’.
28እነርሱ ደግሞ ወደዚህ ሥቃይ ስፍራ እንዳይመጡ ይመስክርላቸው አለ።
29Abraomas atsiliepė: ‘Jie turi Mozę bei pranašus, tegul jų klauso!’
29አብርሃም ግን። ሙሴና ነቢያት አሉአቸው፤ እነርሱን ይስሙ አለው።
30O anas atsakė: ‘Ne, tėve Abraomai! Bet jei kas iš mirusiųjų nueitų pas juos, jie atgailautų!’
30እርሱም። አይደለም፥ አብርሃም አባት ሆይ፥ ነገር ግን ከሙታን አንዱ ቢሄድላቸው ንስሐ ይገባሉ አለ።
31Tačiau Abraomas tarė: ‘Jeigu jie neklauso Mozės ir pranašų, tai nepatikės, jei kas ir iš numirusių prisikeltų’ ”.
31ሙሴንና ነቢያትንም የማይሰሙ ከሆነ፥ ከሙታንም እንኳ አንድ ቢነሣ አያምኑም አለው።