Lithuanian

Amharic: New Testament

Luke

17

1Jėzus kalbėjo savo mokiniams: “Papiktinimai neišvengiami, bet vargas tam, per kurį jie ateina.
1ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ። መሰናክል ግድ ሳይመጣ አይቀርም፥ ነገር ግን መሰናክሉን ለሚያመጣው ወዮለት፤
2Jam būtų geriau, jei ant kaklo užkabintų girnų akmenį ir įmestų jūron, negu jis papiktintų nors vieną iš šitų mažutėlių.
2ከእነዚህ ከታናናሾች አንዱን ከማሰናከል ይልቅ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ባሕር ቢጣል ይጠቅመው ነበር።
3Saugokitės! Jei tavo brolis nusideda prieš tave, sudrausk jį ir, jeigu jis atgailauja, atleisk jam.
3ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ወንድምህ ቢበድልህ ገሥጸው፥ ቢጸጸትም ይቅር በለው።
4Jei jis septynis kartus per dieną tau nusidėtų ir septynis kartus kreiptųsi į tave, sakydamas: ‘Atgailauju’,­atleisk jam”.
4በቀንም ሰባት ጊዜ እንኳ ቢበድልህ በቀንም ሰባት ጊዜ። ተጸጸትሁ እያለ ወደ አንተ ቢመለስ፥ ይቅር በለው።
5Apaštalai tarė Viešpačiui: “Sustiprink mūsų tikėjimą”.
5ሐዋርያትም ጌታን። እምነት ጨምርልን አሉት።
6O Viešpats atsakė: “Jei turėtumėte tikėjimą kaip garstyčios grūdelį, galėtumėte sakyti šitam šilkmedžiui: ‘Išsirauk ir pasisodink jūroje’,­ir jis paklausytų jūsų”.
6ጌታም አለ። የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ሾላ። ተነቅለህ ወደ ባሕር ተተከል ብትሉት፥ ይታዘዝላችሁ ነበር።
7“Kas iš jūsų, turėdamas ariantį ar ganantį vergą, jam grįžus iš lauko, sakys: ‘Tuojau sėsk prie stalo’?
7ከእናንተም የሚያርስ ወይም ከብትን የሚጠብቅ ባሪያ ያለው፥ ከእርሻ ሲመለስ። ወዲያው ቅረብና በማዕድ ተቀመጥ የሚለው ማን ነው?
8Argi nesakys jam: ‘Paruošk man vakarienę. Susijuosk ir patarnauk, kol aš valgysiu ir gersiu, o paskui tu pavalgysi ir atsigersi’?
8የምበላውን እራቴን አሰናዳልኝ፥ እስክበላና እስክጠጣ ድረስ ታጥቀህ አገልግለኝ፥ በኋላም አንተ ብላና ጠጣ የሚለው አይደለምን?
9Argi vergui dėkojama, kad jis atliko tai, kas jam liepta? Nemanau.
9ያንን ባሪያ ያዘዘውን ስላደረገ ያመሰግነዋልን?
10Taigi jūs, atlikę visa, kas jums pavesta, sakykite: ‘Esame nenaudingi vergai. Padarėme, ką privalėjome padaryti’ ”.
10እንዲሁ እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ። የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፥ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል በሉ።
11Keliaujant į Jeruzalę, teko Jėzui eiti tarp Samarijos ir Galilėjos.
11ወደ ኢየሩሳሌምም ሲሄድ በገሊላና በሰማርያ መካከል አለፈ።
12Jam įeinant į vieną kaimą, Jį pasitiko dešimt raupsuotų vyrų. Jie sustojo atstu
12ወደ አንዲት መንደርም ሲገባ በሩቅ የቆሙት አሥር ለምጻሞች ተገናኙት፤
13ir garsiai šaukė: “Jėzau, Mokytojau, pasigailėk mūsų!”
13እነርሱም እየጮኹ። ኢየሱስ ሆይ፥ አቤቱ፥ ማረን አሉ።
14Pamatęs juos, Jis tarė: “Eikite, pasirodykite kunigams!” Ir beeidami jie pasveiko.
14አይቶም። ሂዱ፥ ራሳችሁን ለካህናት አሳዩ አላቸው።
15Vienas iš jų, patyręs, kad išgijo, sugrįžo atgal, garsiai garbindamas Dievą.
15እነሆም፥ ሲሄዱ ነጹ። ከእነርሱም አንዱ እንደ ተፈወሰ ባየ ጊዜ በታላቅ ድምፅ እግዚአብሔርን እያከበረ ተመለሰ፥
16Jis dėkodamas parpuolė Jėzui po kojų. Tai buvo samarietis.
16እያመሰገነውም በእግሩ ፊት በግንባሩ ወደቀ፤ እርሱም ሳምራዊ ነበረ።
17Jėzus paklausė: “Argi ne dešimt pasveiko? Kur dar devyni?
17ኢየሱስም መልሶ። አሥሩ አልነጹምን? ዘጠኙስ ወዴት አሉ?
18Ar neatsirado nė vieno, kuris grįžtų atiduoti Dievui garbę, išskyrus šitą svetimtautį?”
18ከዚህ ከልዩ ወገን በቀር እግዚአብሔርን ሊያከብሩ የተመለሱ አልተገኙም አለ።
19Ir tarė jam: “Kelkis, eik! Tavo tikėjimas išgydė tave”.
19እርሱንም። ተነሣና ሂድ፤ እምነትህ አድኖሃል አለው።
20Fariziejų paklaustas, kada ateis Dievo karalystė, Jėzus atsakė: “Dievo karalystė neateina regimai.
20ፈሪሳውያንም። የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች ብለው ቢጠይቁት፥ መልሶ። የእግዚአብሔር መንግሥት በመጠባበቅ አትመጣም፤
21Niekas nepasakys: ‘Žiūrėk, ji čia’, arba: ‘Žiūrėk, ji ten!’ Nes štai Dievo karalystė yra tarp jūsų”.
21ደግሞም። እንኋት በዚህ ወይም። እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው።
22Ir Jis tarė mokiniams: “Ateis dienos, kai norėsite išvysti bent vieną Žmogaus Sūnaus dieną, ir nepamatysite.
22ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ። ከሰው ልጅ ቀኖች አንዱን ልታዩ የምትመኙበት ወራት ይመጣል አታዩትምም።
23Jums sakys: ‘Žiūrėkite čia! Žiūrėkite ten!’­Nesekite jais ir neikite paskui juos.
23እነርሱም። እነሆ በዚህ፥ ወይም። እነሆ በዚያ ይሉአችኋል፤ አትሂዱ አትከተሉአቸውም።
24Kaip tvykstelėjęs žaibas nušviečia viską nuo vieno dangaus pakraščio iki kito, taip savo dieną pasirodys ir Žmogaus Sūnus.
24መብረቅ በርቆ ከሰማይ በታች ካለ ከአንድ አገር ከሰማይ በታች ወዳለው ወደ ሌላ አገር እንደሚያበራ፥ የሰው ልጅ በቀኑ እንዲህ ይሆናል።
25Bet pirmiau Jis turės daug iškentėti ir būti šitos kartos atmestas.
25አስቀድሞ ግን ብዙ መከራ እንዲቀበል ከዚህም ትውልድ እንዲጣል ይገባዋል።
26Kaip buvo Nojaus dienomis, taip bus ir Žmogaus Sūnaus dienomis.
26በኖኅ ዘመንም እንደ ሆነ፥ በሰው ልጅ ዘመን ደግሞ እንዲሁ ይሆናል።
27Jie valgė, gėrė, tuokėsi ir tuokė, kol atėjo diena, kai Nojus įlipo į laivą. Tada užėjo tvanas ir visus sunaikino.
27ኖኅ ወደ መርከብ እስከ ገባበት ቀን ድረስ፥ ይበሉና ይጠጡ ያገቡና ይጋቡም ነበር፥ የጥፋት ውኃም መጣ ሁሉንም አጠፋ።
28Taip pat buvo ir Loto dienomis. Jie valgė ir gėrė, pirko ir pardavinėjo, sodino ir statė.
28እንዲሁ በሎጥ ዘመን እንደ ሆነ፤ ይበሉ ይጠጡም ይገዙም ይሸጡም ይተክሉም ቤትም ይሠሩ ነበር፤
29O tą dieną, kada Lotas paliko Sodomą, iš dangaus krito ugnis ir siera ir visus sunaikino.
29ሎጥ ከሰዶም በወጣበት ቀን ግን ከሰማይ እሳትና ዲን ዘነበ ሁሉንም አጠፋ።
30Šitaip bus ir tą dieną, kai pasirodys Žmogaus Sūnus.
30የሰው ልጅ በሚገለጥበት ቀን እንዲሁ ይሆናል።
31Kas tą dieną bus ant stogo, o jo daiktai viduje, tenelipa žemyn jų pasiimti, o kas laukuose, tenegrįžta namo.
31በዚያም ቀን በሰገነት ያለ በቤቱ ያለውን ዕቃ ሊወስድ አይውረድ፥ እንዲሁም በእርሻ ያለ ወደ ኋላው አይመለስ።
32Prisiminkite Loto žmoną!
32የሎጥን ሚስት አስቡአት።
33Kas stengsis išgelbėti savo gyvybę, tas ją praras, o kas ją praras, tas atgaivins ją.
33ነፍሱን ሊያድን የሚፈልግ ሁሉ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም የሚያጠፋ ሁሉ በሕይወት ይጠብቃታል።
34Sakau jums: tą naktį dviese miegos vienoje lovoje, ir vienas bus paimtas, o kitas paliktas.
34እላችኋለሁ፥ በዚያች ሌሊት ሁለት ሰዎች በአንድ አልጋ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
35Dvi mals drauge, ir viena bus paimta, o kita palikta.
35ሁለት ሴቶች በአንድ ወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዲቱ ትወሰዳለች ሁለተኛይቱም ትቀራለች።
36Du bus lauke, ir vienas bus paimtas, kitas paliktas”.
36ሁለት ሰዎች በእርሻ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
37Tada jie atsiliepė: “O kurgi, Viešpatie?” Jis atsakė: “Kur tik bus lavonų, ten sulėks ir maitvanagiai”.
37መልሰውም። ጌታ ሆይ፥ ወዴት ነው? አሉት። እርሱም። ሥጋ ወዳለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ አላቸው።