Lithuanian

Amharic: New Testament

Luke

18

1Jėzus pasakė jiems palyginimą, kaip reikia visuomet melstis ir neprarasti ryžto,
1ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥
2tardamas: “Viename mieste buvo teisėjas, kuris nebijojo Dievo ir nesidrovėjo žmonių.
2እንዲህ ሲል። በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ።
3Tame pačiame mieste gyveno našlė, kuri vis eidavo pas jį ir prašydavo: ‘Apgink mane nuo mano priešininko!’
3በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፥ ወደ እርሱም እየመጣች። ከባላጋራዬ ፍረድልኝ ትለው ነበር።
4Jis kurį laiką nenorėjo, bet po to tarė sau: ‘Nors aš Dievo nebijau nei žmonių nesidroviu,
4አያሌ ቀንም አልወደደም፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ። ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ ሰውንም ባላፍር፥
5vis dėlto, kai šita našlė neduoda man ramybės, apginsiu jos teises, kad ji, vienąkart atėjusi, man akių neišdraskytų’ ”.
5ይህች መበለት ስለምታደክመኝ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ እፈርድላታለሁ አለ።
6Ir Viešpats tarė: “Įsidėmėkite, ką pasakė tas neteisusis teisėjas.
6ጌታም አለ። ዓመፀኛው ዳኛ ያለውን ስሙ።
7Tad nejaugi Dievas neapgins savo išrinktųjų, kurie Jo šaukiasi dieną ir naktį, ir dels jiems padėti?
7እግዚአብሔር እንኪያስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለሚታገሣቸውም ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን?
8Sakau jums: Jis apgins jų teises labai greitai. Bet ar atėjęs Žmogaus Sūnus beras žemėje tikėjimą?”
8እላችኋለሁ፥ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል። ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን?
9Tiems, kurie pasitikėjo savo teisumu, o kitus niekino, Jėzus pasakė palyginimą:
9ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ሌሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፥
10“Du žmonės atėjo į šventyklą melstis: vienas­fariziejus, o kitas­muitininkas.
10እንዲህ ሲል። ሁለት ሰዎች ሊጸልዩ ወደ መቅደስ ወጡ፥ አንዱ ፈሪሳዊ ሁለተኛውም ቀራጭ።
11Fariziejus stovėdamas taip sau vienas meldėsi: ‘Dėkoju Tau, Dieve, kad nesu toks, kaip kiti žmonės­plėšikai, sukčiai, svetimautojai­arba kaip šis va muitininkas.
11ፈሪሳዊም ቆሞ በልቡ ይህን ሲጸልይ። እግዚአብሔር ሆይ፥ እንደ ሌላ ሰው ሁሉ፥ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፥ ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ፤
12Aš pasninkauju du kartus per savaitę, duodu dešimtinę iš visko, ką įsigyju’.
12በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጦማለሁ፥ ከማገኘውም ሁሉ አሥራት አወጣለሁ አለ።
13O muitininkas, atokiai stovėdamas, nedrįso nė akių pakelti į dangų, tik, mušdamasis į krūtinę, maldavo: ‘Dieve, būk gailestingas man, nusidėjėliui!’
13ቀራጩ ግን በሩቅ ቆሞ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ሊያነሣ እንኳ አልወደደም፥ ነገር ግን። አምላክ ሆይ፥ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ እያለ ደረቱን ይደቃ ነበር።
14Sakau jums: šitas nuėjo į namus išteisintas, o ne anas. Kiekvienas, kuris save aukština, bus pažemintas, o kuris save žemina, bus išaukštintas”.
14እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱን ግን የሚያዋርድ ከፍ ይላል።
15Jėzui atnešdavo kūdikių, kad Jis juos paliestų. Mokiniai, tai matydami, draudė.
15እንዲዳስሳቸውም ሕፃናትን ደግሞ ወደ እርሱ አመጡ፤ ደቀ መዛሙርቱም አይተው ገሠጹአቸው።
16Bet Jėzus, pasišaukęs vaikučius, tarė: “Leiskite mažutėliams ateiti pas mane ir netrukdykite jiems, nes tokių yra Dievo karalystė.
16ኢየሱስ ግን ሕፃናትን ወደ እርሱ ጠርቶ። ሕፃናት ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተዉአቸው አትከልክሉአቸውም፤ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ እነዚህ ላሉት ናትና።
17Iš tiesų sakau jums: kas nepriims Dievo karalystės kaip kūdikis, niekaip neįeis į ją!”
17እውነት እላችኋለሁ፥ የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደ ሕፃን የማይቀበላት ሁሉ ከቶ አይገባባትም አለ።
18Vienas valdininkas Jį paklausė: “Gerasis Mokytojau, ką turiu daryti, kad paveldėčiau amžinąjį gyvenimą?”
18ከአለቆችም አንዱ። ቸር መምህር፥ የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ? ብሎ ጠየቀው።
19Jėzus jam atsakė: “Kodėl vadini mane geru? Nė vieno nėra gero, tik vienas Dievas.
19ኢየሱስም። ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።
20Įsakymus žinai: ‘Nesvetimauk, nežudyk, nevok, melagingai neliudyk, gerbk savo tėvą ir motiną’ ”.
20ትእዛዛቱን ታውቃለህ፥ አታመንዝር፥ አትግደል፥ አትስረቅ፥ በሐሰት አትመስክር፥ አባትህንና እናትህን አክብር አለው።
21Tas atsakė: “Viso šito laikausi nuo savo jaunystės”.
21እርሱም። ይህን ሁሉ ከሕፃንናቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ አለ።
22Tai išgirdęs, Jėzus jam tarė: “Tau trūksta vieno dalyko: parduok visa, ką turi, išdalink vargšams, ir turėsi turtą danguje. Tada ateik ir sek paskui mane!”
22ኢየሱስም ይህን ሰምቶ። አንዲት ገና ቀርታሃለች፤ ያለህን ሁሉ ሽጠህ ለድሆች ስጥ፥ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ፥ መጥተህም ተከተለኝ አለው።
23Tai išgirdęs, jis nusiminė, nes buvo labai turtingas.
23እርሱ ግን ይህን ሰምቶ እጅግ ባለ ጠጋ ነበርና ብዙ አዘነ።
24Matydamas jį nuliūdusį, Jėzus prabilo: “Kaip sunkiai turintieji turtų įeis į Dievo karalystę!
24ኢየሱስም ብዙ እንዳዘነ አይቶ። ገንዘብ ላላቸው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እንዴት ጭንቅ ይሆናል።
25Lengviau kupranugariui išlįsti pro adatos ausį, negu turtingam įeiti į Dievo karalystę!”
25ባለ ጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ሊገባ ይቀላል አለ።
26Girdėjusieji tai paklausė: “Kas tada gali būti išgelbėtas?”
26የሰሙትም። እንግዲህ ማን ሊድን ይችላል? አሉ።
27Jis atsakė: “Kas neįmanoma žmonėms, įmanoma Dievui”.
27እርሱ ግን። በሰው ዘንድ የማይቻል በእግዚአብሔር ዘንድ ይቻላል አለ።
28Tada Petras tarė: “Štai mes viską palikome ir nusekėme paskui Tave”.
28ጴጥሮስም። እነሆ፥ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ አለ።
29Jėzus atsakė jiems: “Iš tiesų sakau jums: nėra nė vieno, kuris paliko namus ar tėvus, ar brolius, ar žmoną, ar vaikus dėl Dievo karalystės
29እርሱም። እውነት እላችኋለሁ፥ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ቤትን ወይም ወላጆችን ወይም ወንድሞችን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን የተወ፥
30ir kuris jau šiuo metu negautų nepalyginamai daugiau, o būsimajame pasaulyje­amžinojo gyvenimo”.
30በዚህ ዘመን ብዙ እጥፍ በሚመጣውም ዓለም የዘላለምን ሕይወት የማይቀበል ማንም የለም አላቸው።
31Jėzus pasišaukė dvylika ir tarė: “Štai mes einame į Jeruzalę, ir ten išsipildys visa, kas per pranašus parašyta apie Žmogaus Sūnų.
31አሥራ ሁለቱንም ወደ እርሱ አቅርቦ እንዲህ አላቸው። እነሆ፥ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፥ ስለ ሰው ልጅም በነቢያት የተጻፈው ሁሉ ይፈጸማል።
32Jis bus atiduotas pagonims, išjuoktas, paniekintas ir apspjaudytas.
32ለአሕዛብ አሳልፈው ይሰጡታልና፥ ይዘብቱበትማል ያንገላቱትማል ይተፉበትማል፤
33Tie nuplaks Jį ir nužudys, bet trečią dieną Jis prisikels”.
33ከገረፉትም በኋላ ይገድሉታል፥ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል።
34Tačiau jie nieko nesuprato; tų žodžių prasmė jiems liko paslėpta, ir jie nesuvokė, kas buvo sakoma.
34እነርሱም ከዚህ ነገር ምንም አላስተዋሉም፥ ይህም ቃል ተሰውሮባቸው ነበር፥ የተናገረውንም አላወቁም።
35Jam artinantis prie Jericho, šalia kelio sėdėjo neregys elgeta.
35ወደ ኢያሪኮም በቀረበ ጊዜ አንድ ዕውር እየለመነ በመንገድ ዳር ተቀምጦ ነበር።
36Išgirdęs praeinančią minią, jis paklausė, kas tai būtų.
36ሕዝብም ሲያልፍ ሰምቶ። ይህ ምንድር ነው? ብሎ ጠየቀ።
37Jam atsakė, kad praeinąs Jėzus iš Nazareto.
37እነርሱም። የናዝሬቱ ኢየሱስ ያልፋል ብለው አወሩለት።
38Tada jis ėmė šaukti: “Jėzau, Dovydo Sūnau, pasigailėk manęs!”
38እርሱም። የዳዊት ልጅ፥ ኢየሱስ ሆይ፥ ማረኝ እያለ ጮኸ።
39Ėję priekyje draudė jį, kad tylėtų, bet tas dar garsiau šaukė: “Dovydo Sūnau, pasigailėk manęs!”
39በስተ ፊት ይሄዱ የነበሩትም ዝም እንዲል ገሠጹት፤ እርሱ ግን። የዳዊት ልጅ ሆይ፥ ማረኝ እያለ አብዝቶ ጮኸ።
40Jėzus sustojo ir liepė jį atvesti. Jam prisiartinus, paklausė jo:
40ኢየሱስም ቆሞ ወደ እርሱ እንዲያመጡት አዘዘ። በቀረበም ጊዜ። ምን ላደርግልህ ትወዳለህ? ብሎ ጠየቀው።
41“Ko nori, kad tau padaryčiau?”
41እርሱም። ጌታ ሆይ፥ አይ ዘንድ ነው አለው።
42Šis atsakė: “Viešpatie, kad praregėčiau!” Jėzus tarė: “Regėk! Tavo tikėjimas išgydė tave”.
42ኢየሱስም። እይ፤ እምነትህ አድኖሃል አለው።
43Tas iškart praregėjo ir nusekė paskui Jį, garbindamas Dievą. Tai matydami, visi žmonės šlovino Dievą.
43በዚያን ጊዜም አየ፥ እግዚአብሔንም እያከበረ ተከተለው። ሕዝቡም ሁሉ አይተው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።