Lithuanian

Amharic: New Testament

Luke

2

1Tomis dienomis išėjo ciesoriaus Augusto įsakymas surašyti visus valstybės gyventojus.
1በዚያም ወራት ዓለሙ ሁሉ እንዲጻፍ ከአውግስጦስ ቄሣር ትእዛዝ ወጣች።
2Toks pirmasis surašymas buvo padarytas Kvirinui valdant Siriją.
2ቄሬኔዎስ በሶርያ አገር ገዥ በነበረ ጊዜ ይህ የመጀመሪያ ጽሕፈት ሆነ።
3Taigi visi keliavo užsirašyti, kiekvienas į savo miestą.
3ሁሉም እያንዳንዱ ይጻፍ ዘንድ ወደ ከተማው ሄደ።
4Taip pat ir Juozapas ėjo iš Galilėjos miesto Nazareto į Judėją, į Dovydo miestą, vadinamą Betliejumi, nes buvo kilęs iš Dovydo namų ir giminės.
4ዮሴፍም ደግሞ ከዳዊት ቤትና ወገን ስለ ነበረ ከገሊላ ከናዝሬት ከተማ ተነሥቶ ቤተ ልሔም ወደምትባል ወደ ዳዊት ከተማ ወደ ይሁዳ፥ ፀንሳ ከነበረች ከእጮኛው ከማርያም ጋር ይጻፍ ዘንድ ወጣ።
5Jis ėjo užsirašyti kartu su savo sužadėtine Marija, kuri buvo nėščia.
6በዚያም ሳሉ የመውለጃዋ ወራት ደረሰ፥
6Jiems ten esant, atėjo jai metas gimdyti, ir ji pagimdė savo pirmagimį Sūnų,
7የበኵር ልጅዋንም ወለደች፥ በመጠቅለያም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማደሪያ ስፍራ ስላልነበራቸው በግርግም አስተኛችው።
7suvystė Jį vystyklais ir paguldė ėdžiose, nes jiems nebuvo vietos užeigoje.
8በዚያም ምድር መንጋቸውን በሌሊት ሲጠብቁ በሜዳ ያደሩ እረኞች ነበሩ።
8Toje apylinkėje laukuose buvo piemenys, kurie, budėdami naktį, saugojo savo bandą.
9እነሆም፥ የጌታ መልአክ ወደ እነርሱ ቀረበ የጌታ ክብርም በዙሪያቸው አበራ፥ ታላቅ ፍርሃትም ፈሩ።
9Staiga jiems pasirodė Viešpaties angelas, ir juos apšvietė Viešpaties šlovė. Jie labai išsigando,
10መልአኩም እንዲህ አላቸው። እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤
10bet angelas jiems tarė: “Nebijokite! Štai skelbiu jums didelį džiaugsmą, kuris bus visai tautai.
11ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።
11Šiandien Dovydo mieste jums gimė Gelbėtojas. Jis yra Viešpats­Kristus.
12ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ።
12Ir štai jums ženklas: rasite kūdikį, suvystytą ir paguldytą ėdžiose”.
13ድንገትም ብዙ የሰማይ ሠራዊት ከመልአኩ ጋር ነበሩ። እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ።
13Staiga prie angelo pasirodė gausi dangaus kareivija, šlovinanti Dievą:
14ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።
14“Šlovė Dievui aukštybėse, o žemėje ramybė ir palankumas žmonėms!”
15መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ፥ እረኞቹ እርስ በርሳቸው። እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ ተባባሉ።
15Kai angelai nuo jų pakilo į dangų, piemenys kalbėjosi: “Eikime į Betliejų ir pažiūrėkime, kas ten įvyko, ką Viešpats mums paskelbė”.
16ፈጥነውም መጡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ።
16Jie nuskubėjo ir rado Mariją, Juozapą ir kūdikį, paguldytą ėdžiose.
17አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ።
17Pamatę jie apsakė, kas jiems buvo pranešta apie šitą kūdikį.
18የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሩአቸው ነገር አደነቁ፤
18Visi, kurie girdėjo, stebėjosi piemenų pasakojimu.
19ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር።
19Marija įsiminė visus šiuos žodžius, dėdamasi juos širdin.
20እረኞችም እንደ ተባለላቸው ስለ ሰሙትና ስላዩት ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እያከበሩ ተመለሱ።
20Piemenys grįžo atgal, garbindami ir šlovindami Dievą už visa, ką buvo girdėję ir matę, kaip jiems buvo paskelbta.
21ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ፥ በማኅፀን ሳይረገዝ በመልአኩ እንደ ተባለ፥ ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ።
21Praslinkus aštuonioms dienoms, kai reikėjo apipjaustyti vaikelį, Jam buvo duotas Jėzaus vardas, kurį angelas nurodė dar prieš Jo pradėjimą įsčiose.
22እንደ ሙሴም ሕግ የመንጻታቸው ወራት በተፈጸመ ጊዜ፥ በጌታ ሕግ። የእናቱን ማኅፀን የሚከፍት ወንድ ሁሉ ለጌታ የተቀደሰ ይባላል ተብሎ እንደ ተጻፈ በጌታ ፊት ሊያቆሙት፥ በጌታም ሕግ። ሁለት ዋሊያ ወይም ሁለት የርግብ ጫጩቶች እንደ ተባለ፥ መሥዋዕት ሊያቀርቡ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት።
22Pasibaigus Mozės Įstatymo nustatytoms apsivalymo dienoms, jie nunešė Jį į Jeruzalę pašvęsti Viešpačiui,­
25እነሆም፥ በኢየሩሳሌም ስምዖን የሚባል ሰው ነበረ፥ ይህም ሰው የእስራኤልን መጽናናት ይጠባበቅ ነበር፤ ጻድቅና ትጉህም ነበረ፥ መንፈስ ቅዱስም በእርሱ ላይ ነበረ።
23kaip parašyta Viešpaties Įstatyme: “Kiekvienas pirmagimis berniukas bus atskirtas Viešpačiui”,­
26በጌታም የተቀባውን ሳያይ ሞትን እንዳያይ በመንፈስ ቅዱስ ተረድቶ ነበር።
24ir duoti auką, kaip pasakyta Viešpaties Įstatyme: “Porą purplelių arba du balandžiukus”.
27በመንፈስም ወደ መቅደስ ወጣ፤ ወላጆቹም እንደ ሕጉ ልማድ ያደርጉለት ዘንድ ሕፃኑን ኢየሱስን በአስገቡት ጊዜ፥
25Jeruzalėje gyveno žmogus, vardu Simeonas, teisus ir dievobaimingas vyras, kuris laukė Izraelio paguodos, ir Šventoji Dvasia buvo ant jo.
28እርሱ ደግሞ ተቀብሎ አቀፈው እግዚአብሔርንም እየባረከ እንዲህ አለ።
26Jam buvo apreikšta Šventąja Dvasia, kad jis nemirsiąs, kol pamatysiąs Viešpaties Kristų.
29ጌታ ሆይ፥ አሁን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ፤
27Dvasios paragintas, jis atėjo į šventyklą. Įnešant tėvams kūdikį Jėzų, kad pasielgtų su Juo, kaip Įstatymas reikalauja,
30ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና፤
28Simeonas paėmė Jį į rankas, laimino Dievą ir tarė:
32ይህም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን ለሕዝብህም ለእስራኤል ክብር ነው።
29“Dabar, Valdove, leidi, kaip žadėjai, savo tarnui ramiai iškeliauti,
33ዮሴፍና እናቱም ስለ እርሱ በተባለው ነገር ይደነቁ ነበር።
30nes mano akys išvydo Tavo išgelbėjimą,
34ስምዖንም ባረካቸው እናቱን ማርያምንም። እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥ በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት።
31kurį paruošei visų tautų akivaizdoje:
36ከአሴር ወገንም የምትሆን የፋኑኤል ልጅ ሐና የምትባል አንዲት ነቢይት ነበረች፤ እርስዋም ከድንግልናዋ ጀምራ ከባልዋ ጋር ሰባት ዓመት ኖረች፤
32šviesą pagonims apšviesti ir Tavo Izraelio tautos šlovę”.
37እርስዋም ሰማኒያ አራት ዓመት ያህል መበለት ሆና በጣም አርጅታ ነበር፤ በጾምና በጸሎትም ሌሊትና ቀን እያገለገለች ከመቅደስ አትለይም ነበር።
33Juozapas ir Jėzaus motina stebėjosi tuo, kas buvo apie Jį kalbama.
38በዚያችም ሰዓት ቀርባ እግዚአብሔርን አመሰገነች፤ የኢየሩሳሌምንም ቤዛ ለሚጠባበቁ ሁሉ ስለ እርሱ ትናገር ነበር።
34Simeonas palaimino juos ir tarė Marijai, Jo motinai: “Štai šis skirtas daugelio Izraelyje nupuolimui ir atsikėlimui. Jis bus prieštaravimo ženklas,­
39ሁሉንም እንደ ጌታ ሕግ ከፈጸሙ በኋላ፥ ወደ ገሊላ ወደ ከተማቸው ወደ ናዝሬት ተመለሱ።
35ir tavo pačios sielą pervers kalavijas,­kad būtų atskleistos daugelio širdžių mintys”.
40ሕፃኑም አደገ፥ ጥበብም ሞልቶበት በመንፈስ ጠነከረ፤ የእግዚአብሔርም ጸጋ በእርሱ ላይ ነበረ።
36Ten buvo ir pranašė Ona, Fanuelio duktė iš Asero giminės. Ji buvo seno amžiaus. Po mergystės ji išgyveno septynerius metus su vyru,
41ወላጆቹም በያመቱ በፋሲካ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ይወጡ ነበር።
37o paskui našlaudama sulaukė aštuoniasdešimt ketverių metų. Ji nesitraukdavo nuo šventyklos, tarnaudama Dievui per dienas ir naktis pasninkais bei maldomis.
42የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ በሆነ ጊዜ፥ እንደ በዓሉ ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ፤
38Ir ji, tuo pačiu metu priėjusi, dėkojo Dievui ir kalbėjo apie kūdikį visiems, kurie laukė Jeruzalės atpirkimo.
43ቀኖቹንም ከፈጸሙ በኋላ፥ ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፥ ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር።
39Atlikę visa, ko reikalavo Viešpaties Įstatymas, jie sugrįžo į Galilėją, į savo miestą Nazaretą.
44ከመንገደኞች ጋር የነበረ ስለ መሰላቸው የአንድ ቀን መንገድ ሄዱ፥ ከዘመዶቻቸውም ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፈለጉት፤
40Vaikelis augo, stiprėjo dvasia, buvo pilnas išminties, ir Dievo malonė buvo su Juo.
45ባጡትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ።
41Jo tėvai kasmet eidavo į Jeruzalę švęsti Paschos.
46ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም በመቅደስ አገኙት፤
42Kai Jėzui sukako dvylika metų, šventės papročiu jie nuvyko į Jeruzalę.
47የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ተገረሙ።
43Pasibaigus šventės dienoms ir jiems grįžtant atgal, vaikas Jėzus pasiliko Jeruzalėje, bet Juozapas ir Jo motina to nepastebėjo.
48ባዩትም ጊዜ ተገረሙ፥ እናቱም። ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን አለችው።
44Manydami Jį esant keleivių būryje, jie, nuėję dienos kelią, pradėjo ieškoti Jo tarp giminių ir pažįstamų.
49እርሱም። ስለ ምን ፈለጋችሁኝ? በአባቴ ቤት እሆን ዘንድ እንዲገባኝ አላወቃችሁምን? አላቸው።
45Nesuradę grįžo Jo beieškodami į Jeruzalę.
50እነርሱም የተናገራቸውን ነገር አላስተዋሉም።
46Pagaliau po trijų dienų rado Jį šventykloje, sėdintį tarp mokytojų, besiklausantį jų ir juos beklausinėjantį.
51ከእነርሱም ጋር ወርዶ ወደ ናዝሬት መጣ፥ ይታዘዝላቸውም ነበር። እናቱም ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ ትጠብቀው ነበር።
47Visi, kurie Jį girdėjo, stebėjosi Jo išmanymu ir atsakymais.
52ኢየሱስም ደግሞ በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር።
48Pamatę Jį, jie labai nustebo, ir Jo motina Jam tarė: “Vaikeli, kodėl mums taip padarei? Štai Tavo tėvas ir aš sielvartaudami ieškojome Tavęs”.
49Jis atsakė: “Kam gi manęs ieškojote? Argi nežinote, kad man reikia būti savo Tėvo reikaluose?”
50Bet jie nesuprato Jo pasakytų žodžių.
51Jis iškeliavo su jais ir grįžo į Nazaretą; ir buvo jiems klusnus. Jo motina laikė visus tuos žodžius savo širdyje.
52O Jėzus augo išmintimi, metais ir malone Dievo ir žmonių akyse.