1Pažvelgęs Jis pamatė turtinguosius, dedančius savo dovanas į iždinę.
1ዓይኑንም አንሥቶ መባቸውን በመዝገብ የሚጥሉ ባለ ጠጎችን አየ።
2Jis pamatė ir vieną beturtę našlę, kuri įmetė du smulkius pinigėlius.
2አንዲትም ድሀ መበለት ሁለት ሳንቲም በዚያ ስትጥል አየና።
3Ir Jis tarė: “Iš tiesų sakau jums, ši beturtė našlė įmetė daugiau už visus.
3እውነት እላችኋለሁ፥ ይህች ድሀ መበለት ከሁሉ ይልቅ አብልጣ ጣለች፤
4Nes anie visi iš savo pertekliaus aukojo dovanų Dievui, o ji iš savo nepritekliaus įmetė viską, ką turėjo pragyvenimui”.
4እነዚህ ሁሉ ከትርፋቸው ወደ እግዚአብሔር መዝገብ ጥለዋልና፤ ይህች ግን ከጕድለትዋ የነበራትን ትዳርዋን ሁሉ ጣለች አለ።
5Kai kuriems kalbant apie šventyklą, kad ji išpuošta gražiais akmenimis bei dovanomis, Jėzus prabilo:
5አንዳንዶቹም ስለ መቅደስ በመልካም ድንጋይና በተሰጠው ሽልማት እንዳጌጠ ሲነጋገሩ። ይህማ የምታዩት ሁሉ፥
6“Ateis dienos, kai iš to, ką matote, neliks akmens ant akmens, viskas bus išgriauta”.
6ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ የማይቀርበት ዘመን ይመጣል አለ።
7Jie paklausė: “Mokytojau, kada tai įvyks? Ir koks bus ženklas, kai visa tai pradės pildytis?”
7እነርሱም። መምህር ሆይ፥ እንግዲህ ይህ መቼ ይሆናል? ይህስ ይሆን ዘንድ እንዳለው ምልክቱ ምንድር ነው? ብለው ጠየቁት።
8Jis pasakė: “Žiūrėkite, kad nebūtumėte suklaidinti, nes daugelis ateis mano vardu, ir sakys: ‘Tai Aš!’ ir: ‘Atėjo metas!’ Neikite paskui juos!
8እንዲህም አለ። እንዳትስቱ ተጠንቀቁ፤ ብዙዎች። እኔ ነኝ፥ ዘመኑም ቀርቦአል እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ እነርሱን ተከትላችሁ አትሂዱ።
9O kai išgirsite apie karus ir maištus, nenusigąskite, nes visa tai turi pirmiau įvykti, bet dar negreit galas”.
9ጦርንና ሁከትንም በሰማችሁ ጊዜ አትደንግጡ፤ ይህ አስቀድሞ ይሆን ዘንድ ግድ ነውና፥ ነገር ግን መጨረሻው ወዲያው አይሆንም።
10Ir dar jiems sakė: “Tauta sukils prieš tautą ir karalystė prieš karalystę.
10በዚያን ጊዜ እንዲህ አላቸው። ሕዝብ በሕዝብ ላይ፥ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣል፤
11Įvairiose vietose bus didelių žemės drebėjimų, badmečių, marų, bus baisių įvykių ir didelių ženklų iš dangaus.
11ታላቅም የምድር መናወጥና በልዩ ልዩ ስፍራ ቸነፈር ራብም ይሆናል፤ የሚያስፈራም ነገር ከሰማይም ታላቅ ምልክት ይሆናል።
12Bet prieš tai jie pakels prieš jus rankas ir dėl mano vardo jus persekios, tempdami į sinagogas ir kalėjimus, ves pas karalius ir valdytojus.
12ከዚህም ሁሉ በፊት እጃቸውን በላያችሁ ይጭናሉ ያሳድዱአችሁማል፤ ስለ ስሜም ወደ ምኵራብና ወደ ወኅኒ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ወደ ነገሥታትና ወደ ገዥዎችም ይወስዱአችኋል፤
13Tai bus jums proga liudyti.
13ይህም ለምስክርነት ይሆንላችኋል።
14Taigi įsidėkite sau į širdis iš anksto negalvoti, kaip ginsitės,
14ሰለዚህ እንዴት እንድትመልሱ አስቀድማችሁ እንዳታስቡ በልባችሁ አኑሩት፤
15nes Aš jums duosiu tokios iškalbos ir išminties, kad nė vienas jūsų priešininkas negalės nei atsispirti, nei prieštarauti.
15ወደረኞቻችሁ ሁሉ ሊቃወሙና ሊከራከሩ የማይችሉትን አፍና ጥበብ እሰጣችኋለሁና።
16Jus išdavinės tėvai, broliai, giminės ir draugai; kai kuriuos iš jūsų jie žudys.
16ወላጆችም ስንኳ ወንድሞችም ዘመዶችም ወዳጆችም አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ከእናንተም አንዳንዱን ይገድላሉ፤
17Būsite visų nekenčiami dėl mano vardo.
17በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።
18Tačiau nė plaukas nuo jūsų galvos nenukris.
18ከራሳችሁም አንዲት ጠጉር ስንኳ አትጠፋም፤
19Savo ištverme išlaikykite savo sielas”.
19በመታገሣችሁም ነፍሳችሁን ታገኛላችሁ።
20“Kai pamatysite Jeruzalę supamą kariuomenės, žinokite, jog prisiartino jos sunaikinimas.
20ኢየሩሳሌም ግን በጭፍራ ተከባ ስታዩ በዚያን ጊዜ ጥፋትዋ እንደ ቀረበ እወቁ።
21Tada, kas bus Judėjoje, tebėga į kalnus, kas miesteteišeina iš jo, kas apylinkėsetenegrįžta.
21የዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራራዎች ይሽሹ፥ በመካከልዋም ያሉ ከእርስዋ ፈቀቅ ይበሉ፥ በገጠር ያሉም ወደ እርስዋ አይግቡ፤
22Nes tai bus bausmės dienos, kad išsipildytų visa, kas parašyta.
22የተጻፈው ሁሉ እንዲፈጸም ይህ የበቀል ጊዜ ነውና።
23Vargas nėščioms ir žindančioms tomis dienomis! Nes baisi nelaimė ir rūstybė ištiks šitą tautą.
23በዚያን ወራት ለእርጕዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው፤ ታላቅ ችግር በምድር ላይ፥ በዚህም ሕዝብ ላይ ቍጣ ይሆናልና፤
24Žmonės kris nuo kalavijo ašmenų ir bus išvaryti nelaisvėn į visas tautas, o Jeruzalę mindžios pagonys, kol baigsis pagonių laikai”.
24በሰይፍ ስለትም ይወድቃሉ፤ ወደ አሕዛብ ሁሉም ይማረካሉ፤ የአሕዛብም ዘመን እስኪፈጸም ድረስ ኢየሩሳሌም በአሕዛብ የተረገጠች ትሆናለች።
25“Bus ženklų saulėje, mėnulyje ir žvaigždėse, o žemėje blaškysis sielvarto slegiamos tautos, jūrai baisiai šniokščiant ir šėlstant.
25በፀሐይና በጨረቃም በከዋክብትም ምልክት ይሆናል፤ በምድር ላይም አሕዛብ ከባሕሩና ከሞገዱም ድምፅ የተነሣ እያመነቱ ይጨነቃሉ፤
26Žmonės sustings iš baimės, laukdami to, kas turės ištikti pasaulį, nes dangaus galybės bus sudrebintos.
26ሰዎችም ከፍርሃትና በዓለም የሚመጣበትን ከመጠበቅ የተነሣ ይደክማሉ፤ የሰማያት ኃይላት ይናወጣሉና።
27Tada jie išvys Žmogaus Sūnų, ateinantį debesyje su jėga ir didžia šlove.
27በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በኃይልና በብዙ ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል።
28Kai tai prasidės, atsitieskite ir pakelkite galvas, nes artėja jūsų atpirkimas”.
28ይህም ሊሆን ሲጀምር ቤዛችሁ ቀርቦአልና አሻቅባችሁ ራሳችሁን አንሡ።
29Ir Jis jiems pasakė palyginimą: “Stebėkite figmedį bei visus kitus medžius.
29ምሳሌንም ነገራቸው እንዲህ ሲል። በለስንና ዛፎችን ሁሉ እዩ፤
30Kai jie ima sprogti, jūs patys matote ir žinote, kad vasara jau arti.
30ሲያቈጠቍጡ ተመልክታችሁ በጋ አሁን እንደ ቀረበ ራሳችሁ ታውቃላችሁ።
31Taip pat pamatę visa tai vykstant, žinokite, kad arti yra Dievo karalystė.
31እንዲሁ ደግሞ እናንተ ይህ ሁሉ መሆኑን ስታዩ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ ቀረበች እወቁ።
32Iš tiesų sakau jums: ši karta nepraeis, iki visa tai įvyks.
32እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም።
33Dangus ir žemė praeis, o mano žodžiai nepraeis.
33ሰማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን አያልፍም።
34Saugokitės, kad jūsų širdys nebūtų apsunkintos nesaikingumo, girtavimo ir gyvenimo rūpesčių, kad toji diena neužkluptų jūsų netikėtai.
34ነገር ግን ልባችሁ በመጠጥ ብዛትና በስካር ስለ ትዳርም በማሰብ እንዳይከብድ፥ ያ ቀንም በድንገት እንዳይመጣባችሁ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤
35It žabangai ji užgrius visus žemės gyventojus.
35በምድር ሁሉ ላይ በሚቀመጡ ሁሉ እንደ ወጥመድ ይደርስባቸዋልና።
36Todėl visą laiką budėkite ir melskitės, kad būtumėt palaikyti vertais išvengti visko, kas įvyks, ir stoti prieš Žmogaus Sūnų”.
36እንግዲህ ሊመጣ ካለው ከዚህ ሁሉ ለማምለጥ፥ በሰው ልጅም ፊት ለመቆም እንድትችሉ ስትጸልዩ ሁል ጊዜ ትጉ።
37Taip Jėzus dienomis mokydavo šventykloje, o naktis praleisdavo vadinamajame Alyvų kalne.
37ዕለት ዕለትም በመቅደስ ያስተምር ነበር፥ ሌሊት ግን ደብረ ዘይት ወደምትባል ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር።
38Ir nuo ankstyvo ryto visi žmonės rinkdavosi Jo pasiklausyti šventykloje.
38ሕዝቡም ሁሉ ይሰሙት ዘንድ ማልደው በመቅደስ ወደ እርሱ ይመጡ ነበር።