Lithuanian

Amharic: New Testament

Luke

22

1Artėjo Neraugintos duonos šventė, vadinama Pascha.
1ፋሲካም የሚባለው የቂጣ በዓል ቀረበ።
2Aukštieji kunigai ir Rašto žinovai ieškojo būdo nužudyti Jėzų, nes bijojo žmonių.
2የካህናት አለቆችና ጻፎችም እንዴት እንዲያጠፉት ይፈልጉ ነበር፤ ሕዝቡን ይፈሩ ነበርና።
3O šėtonas įėjo į Judą, vadinamą Iskarijotu, vieną iš dvylikos.
3ሰይጣንም ከአሥራ ሁለቱ ቍጥር አንዱ በነበረው የአስቆሮቱ በሚባለው በይሁዳ ገባ፤
4Tas nuėjęs tarėsi su aukštaisiais kunigais ir sargybos viršininkais, kaip Jį išduoti.
4ሄዶም እንዴት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ከካህናት አለቆችና ከመቅደስ አዛዦች ጋር ተነጋገረ።
5Šie apsidžiaugė ir sutarė duoti jam pinigų.
5እነርሱም ደስ አላቸው፥ ገንዘብም ሊሰጡት ተዋዋሉ።
6Judas pažadėjo ir ieškojo progos išduoti jiems Jėzų, miniai nematant.
6እሺም አለ፥ ሕዝብም በሌለበት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ምቹ ጊዜ ይፈልግ ነበር።
7Atėjo Neraugintos duonos diena, kada reikėjo pjauti Paschos avinėlį.
7ፋሲካንም ሊያርዱበት የሚገባው የቂጣ በዓል ደረሰ፤
8Jėzus pasiuntė Petrą ir Joną, liepdamas: “Eikite ir paruoškite mums valgyti Paschą”.
8ጴጥሮስንና ዮሐንስንም። ፋሲካን እንድንበላ ሄዳችሁ አዘጋጁልን ብሎ ላካቸው።
9Jie paklausė: “Kur nori, kad paruoštume?”
9እነርሱም። ወዴት እናዘጋጅ ዘንድ ትወዳለህ? አሉት።
10Jis atsakė: “Štai jums įeinant į miestą, jus pasitiks žmogus, vandens ąsočiu nešinas. Sekite paskui jį iki tų namų, į kuriuos jis įeis,
10እርሱም አላቸው። እነሆ፥ ወደ ከተማ ስትገቡ ማድጋ ውኃ የተሸከመ ሰው ይገናኛችኋል፤ ወደ ሚገባበት ቤት ተከተሉት፤
11ir sakykite namų šeimininkui: ‘Mokytojas liepė paklausti: Kur svečių kambarys, kuriame galėčiau su mokiniais valgyti Paschą?’
11ለባለቤቱም። መምህሩ። ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ፋሲካን የምበላበት የእንግዳ ቤት ክፍል ወዴት ነው? ይልሃል በሉት፤
12Jis parodys jums didelį apstatytą aukštutinį kambarį. Ten ir paruoškite”.
12ያም በደርብ ላይ ያለውን የተነጠፈ ታላቅ አዳራሽ ያሳያችኋል፤ በዚያም አሰናዱልን።
13Nuėję jie rado viską, kaip Jis sakė, ir paruošė Paschą.
13ሄደውም እንዳላቸው አገኙና ፋሲካን አሰናዱ።
14Atėjus metui, Jis sėdo prie stalo, ir dvylika apaštalų drauge su Juo.
14ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር በማዕድ ተቀመጠ።
15Ir Jis tarė jiems: “Trokšte troškau valgyti su jumis šią Paschą prieš kentėdamas.
15እርሱም። ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤
16Sakau jums, nuo šiol daugiau jos nebevalgysiu, kol ji išsipildys Dievo karalystėje”.
16እላችኋለሁና፥ በእግዚአብሔር መንግሥት እስኪፈጸም ድረስ፥ ወደ ፊት ከዚህ አልበላም አላቸው።
17Paėmęs taurę, Jis padėkojo ir tarė: “Imkite ir dalykitės.
17ጽዋንም ተቀበለ አመስግኖም። ይህን እንካችሁ በመካከላችሁም ተካፈሉት፤
18Sakau jums: Aš nebegersiu vynmedžio vaisiaus, kol ateis Dievo karalystė”.
18እላችኋለሁና፥ የእግዚአብሔር መንግሥት እስክትመጣ ድረስ ከአሁን ጀምሮ ከወይኑ ፍሬ አልጠጣም አለ።
19Ir, paėmęs duoną, Jis padėkojo, laužė ją ir davė jiems, sakydamas: “Tai yra mano kūnas, kuris už jus atiduodamas. Tai darykite mano atminimui”.
19እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና። ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
20Lygiai taip po vakarienės Jis paėmė taurę, sakydamas: “Ši taurė yra Naujoji Sandora mano kraujyje, kuris už jus išliejamas.
20እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ እንዲህ አለ። ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው።
21Bet štai mano išdavėjo ranka yra kartu su manąja ant stalo.
21ነገር ግን አሳልፎ የሚሰጠኝ እጅ እነሆ በማዕድ ከእኔ ጋር ናት።
22Žmogaus Sūnus, tiesa, eina, kaip Jam paskirta, bet vargas tam žmogui, kuris Jį išduoda!”
22የሰው ልጅስ እንደ ተወሰነው ይሄዳል፥ ነገር ግን አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት።
23Tada jie pradėjo klausinėti vienas kito, kas gi iš jų yra tas, kuris tai padarys.
23ከእነርሱም ይህን ሊያደርግ ያለው ማን እንደ ሆነ እርስ በርሳቸው ይጠያየቁ ጀመር።
24Tarp jų taip pat kilo ginčas, kuris iš jų turėtų būti laikomas didžiausiu.
24ደግሞም ማናቸውም ታላቅ ሆኖ እንዲቈጠር በመካከላቸው ክርክር ሆነ።
25Bet Jėzus jiems pasakė: “Pagonių karaliai viešpatauja jiems ir tie, kurie juos valdo, vadinami geradariais.
25እንዲህም አላቸው። የአሕዛብ ነገሥታት ይገዙአቸዋል፥ በላያቸውም የሚሠለጥኑት ቸርነት አድራጊዎች ይባላሉ።
26Jūs taip nedarykite. Kas didžiausias tarp jūsų, tebūnie tarsi mažiausias, o vadovaujantis tebūnie kaip tarnas.
26እናንተ ግን እንዲህ አትሁኑ፤ ነገር ግን ከእናንተ ታላቅ የሆነ በመካከላችሁ እንደ ታናሽ፥ የሚገዛም እንደሚያገለግል ይሁን።
27Katras yra didesnis­kuris sėdi už stalo ar kuris jam patarnauja? Argi ne tas, kuris sėdi? O Aš tarp jūsų esu kaip tas, kuris patarnauja.
27በማዕድ የተቀመጠ ወይስ የሚያገለግል ማናቸው ታላቅ ነው? የተቀመጠው አይደለምን? እኔ ግን በመካከላችሁ እንደሚያገለግል ነኝ።
28Jūs ištvėrėte su manimi mano išbandymuose,
28ነገር ግን እናንተ በፈተናዎቼ ከእኔ ጋር ጸንታችሁ የኖራችሁ ናችሁ፤
29todėl Aš jums skiriu valdyti karalystę, kaip ir man yra skyręs Tėvas,
29አባቴ እኔን እንደ ሾመኝ እኔ ደግሞ በመንግሥቴ ከማዕዴ ትበሉና ትጠጡ ዘንድ፥ በአሥራ ሁለቱ በእስራኤል ነገድ ስትፈርዱ በዙፋኖች ትቀመጡ ዘንድ ለመንግሥት እሾማችኋለሁ።
30kad mano karalystėje jūs valgytumėte ir gertumėte už mano stalo ir sėdėtumėte sostuose, teisdami dvylika Izraelio giminių”.
31ጌታም። ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤
31Ir Viešpats tarė: “Simonai, Simonai! Štai šėtonas prašė persijoti jus tarsi kviečius.
32እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አጽና አለ።
32Bet Aš meldžiau už tave, kad tavo tikėjimas nepalūžtų, ir tu atsivertęs stiprink savo brolius!”
33እርሱም። ጌታ ሆይ፥ ወደ ወኅኒም ወደ ሞትም ከአንተ ጋር ለመሄድ የተዘጋጀሁ ነኝ አለው።
33Petras atsiliepė: “Viešpatie, aš pasiruošęs kartu su Tavimi eiti ir į kalėjimą, ir į mirtį!”
34እርሱ ግን። ጴጥሮስ ሆይ፥ እልሃለሁ፥ እንዳታውቀኝ ሦስት ጊዜ እስክትክደኝ ድረስ ዛሬ ዶሮ አይጮኽም አለው።
34Bet Jėzus atsakė: “Sakau tau, Petrai: dar šiandien, gaidžiui nepragydus, tu tris kartus išsiginsi, kad mane pažįsti”.
35ደግሞም። ያለ ኮረጆና ያለ ከረጢት ያለ ጫማም በላክኋችሁ ጊዜ፥ አንዳች ጐደለባችሁን? አላቸው። እነርሱም። አንዳች እንኳ አሉ።
35Jis paklausė juos: “Ar jums ko nors trūko, kai buvau jus išsiuntęs be piniginės, be krepšio ir be sandalų?” Jie atsakė: “Nieko”.
36እርሱም። አሁን ግን ኮረጆ ያለው ከእርሱ ጋር ይውሰድ፥ ከረጢትም ያለው እንዲሁ፤ የሌለውም ልብሱን ሽጦ ሰይፍ ይግዛ።
36Tada Jis jiems tarė: “Dabar, kas turi piniginę, tepasiima ją, taip pat ir krepšį, o kas neturi kalavijo, teparduoda apsiaustą ir tenusiperka.
37እላችኋለሁና፥ ይህ። ከዓመፀኞች ጋር ተቈጠረ ተብሎ የተጻፈው በእኔ ሊፈጸም ግድ ነው፤ አዎን፥ ስለ እኔ የሚሆነው አሁን ይፈጸማልና አላቸው።
37Sakau jums, manyje privalo išsipildyti, kas parašyta: ‘Jis buvo priskaitytas prie piktadarių’; tai, kas man nustatyta, jau eina į pabaigą”.
38እነርሱም። ጌታ ሆይ፥ እነሆ፥ በዚህ ሁለት ሰይፎች አሉ አሉት። እርሱም። ይበቃል አላቸው።
38Jie tarė: “Viešpatie, štai čia du kalavijai!” Jis atsakė: “Gana!”
39ወጥቶም እንደ ልማዱ ወደ ደብረ ዘይት ሄደ፤ ደቀ መዛሙርቱም ደግሞ ተከተሉት።
39Išėjęs iš ten, Jis, kaip buvo pratęs, pasuko į Alyvų kalną. Paskui Jį nuėjo ir mokiniai.
40ወደ ስፍራውም ደርሶ። ወደ ፈተና እንዳትገቡ ጸልዩ አላቸው።
40Atėjus į vietą, Jis tarė jiems: “Melskitės, kad nepakliūtumėte į pagundymą!”
41ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ የሚያህል ራቀ፥ ተንበርክኮም። አባት ሆይ፥
41Ir Jis atsitolino nuo jų maždaug per akmens metimą ir atsiklaupęs ėmė melstis:
42ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር።
42“Tėve, jei nori, atimk šitą taurę nuo manęs, tačiau tebūna ne mano, bet Tavo valia!”
43ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታ መልአክ ታየው።
43Jam pasirodė iš dangaus angelas ir Jį sustiprino.
44በፍርሃትም ሲጣጣር አጽንቶ ይጸልይ ነበር፤ ወዙም በምድር ላይ እንደሚወርድ እንደ ደም ነጠብጣብ ነበረ።
44Vidinės kovos draskomas, Jis dar karščiau meldėsi. Jo prakaitas pasidarė tarsi tiršto kraujo lašai, varvantys žemėn.
45ከጸሎትም ተነሥቶ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጣና ከኀዘን የተነሣ ተኝተው ሲያገኛቸው።
45Atsikėlęs po maldos, Jis atėjo pas mokinius ir rado juos iš sielvarto užmigusius.
46ስለ ምን ትተኛላችሁ? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተነሥታችሁ ጸልዩ አላቸው።
46Jis tarė jiems: “Kodėl miegate? Kelkitės ir melskitės, kad nepakliūtumėte į pagundymą!”
47ገናም ሲናገር እነሆ፥ ሰዎች መጡ፤ ከአሥራ ሁለቱ አንዱም ይሁዳ የሚባለው ይቀድማቸው ነበር፥ ሊስመውም ወደ ኢየሱስ ቀረበ።
47Jam dar tebekalbant, štai pasirodė minia, o priekyje­vienas iš dvylikos, vadinamas Judu. Jis priėjo prie Jėzaus Jo pabučiuoti.
48ኢየሱስ ግን። ይሁዳ ሆይ፥ በመሳም የሰውን ልጅ አሳልፈህ ትሰጣለህን? አለው።
48Jėzus jam tarė: “Judai, pabučiavimu išduodi Žmogaus Sūnų?”
49በዙሪያውም የነበሩት የሚሆነውን ባዩ ጊዜ። ጌታ ሆይ፥ በሰይፍ እንምታቸውን? አሉት።
49Esantieji su Juo, matydami, kas bus, paklausė: “Viešpatie, gal mums kirsti kalaviju?”
50ከእነርሱም አንዱ የሊቀ ካህናቱን ባሪያ መትቶ ቀኝ ጆሮውን ቈረጠው።
50Vienas iš jų smogė vyriausiojo kunigo tarnui ir nukirto jam dešinę ausį.
51ኢየሱስ ግን መልሶ። ይህንስ ፍቀዱ አለ፤ ጆሮውንም ዳስሶ ፈወሰው።
51Bet Jėzus sudraudė: “Liaukitės! Užteks!” Ir palietęs tarno ausį, išgydė jį.
52ኢየሱስም ወደ እርሱ ለመጡበት ለካህናት አለቆችና ለመቅደስ አዛዦች ለሽማግሌዎችም። ወንበዴን እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ወጣችሁን?
52Atėjusiems aukštiesiems kunigams, šventyklos apsaugos viršininkams ir vyresniesiems Jis pasakė: “Kaip prieš plėšiką išėjote prieš mane su kalavijais ir vėzdais.
53በመቅደስ ዕለት ዕለት ከእናንተ ጋር ስሆን እጆቻችሁን አልዘረጋችሁብኝም፤ ይህ ግን ጊዜያችሁና የጨለማው ሥልጣን ነው አላቸው።
53Kai buvau kasdien su jumis šventykloje, jūs nepakėlėte prieš mane rankos. Bet ši valanda jūsų, tamsos valdžia”.
54ይዘውም ወሰዱት ወደ ሊቀ ካህናት ቤትም አገቡት፤ ጴጥሮስም ርቆ ይከተለው ነበር።
54Suėmę Jėzų, jie nusivedė Jį ir atvedė į vyriausiojo kunigo namus. Petras sekė iš tolo.
55በግቢ መካከልም እሳት አንድደው በአንድነት ተቀምጠው ሳሉ ጴጥሮስ በመካከላቸው ተቀመጠ።
55Susikūrę ugnį kiemo viduryje, jie susėdo. Petras atsisėdo kartu.
56በብርሃኑም በኩል ተቀምጦ ሳለ አንዲት ገረድ አየችውና ትኵር ብላ። ይህ ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበረ አለች።
56Viena tarnaitė, pamačiusi jį sėdintį prieš šviesą, įsižiūrėjo ir tarė: “Ir šitas buvo kartu su Juo”.
57እርሱ ግን። አንቺ ሴት፥ አላውቀውም ብሎ ካደ።
57Bet jis išsigynė, sakydamas: “Moterie, nepažįstu Jo!”
58ከጥቂት ጊዜም በኋላ ሌላው አይቶት። አንተ ደግሞ ከእነርሱ ወገን ነህ አለው። ጴጥሮስ ግን። አንተ ሰው፥ እኔ አይደለሁም አለ።
58Truputį vėliau kažkas kitas, jį pamatęs, tarė: “Ir tu esi iš jų”. Petras atsakė: “Ne, žmogau, nesu!”
59አንድ ሰዓትም የሚያህል ቆይቶ ሌላው አስረግጦ። እርሱ የገሊላ ሰው ነውና በእውነት ይህ ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበረ አለ።
59Maždaug po valandos dar vienas ėmė tvirtinti, sakydamas: “Tikrai šitas buvo su Juo! Juk jis galilėjietis!”
60ጴጥሮስ ግን። አንተ ሰው፥ የምትለውን አላውቅም አለ። ያን ጊዜም ገና ሲናገር ዶሮ ጮኸ።
60Petras atsakė: “Žmogau, aš nesuprantu, ką tu sakai”. Ir tuoj pat, dar jam kalbant, pragydo gaidys.
61ጌታም ዘወር ብሎ ጴጥሮስን ተመለከተው፤ ጴጥሮስም። ዛሬ ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ እንዳለው የጌታ ቃል ትዝ አለው።
61Tada Viešpats atsigręžęs pažvelgė į Petrą. Ir Petras atsiminė Viešpaties žodį, kaip Jis buvo jam pasakęs: “Dar gaidžiui nepragydus, tu tris kartus manęs išsiginsi”.
62ጴጥሮስም ወደ ውጭ ወጥቶ ምርር ብሎ አለቀሰ።
62Petras išėjo laukan ir karčiai pravirko.
63ኢየሱስንም የያዙት ሰዎች ይዘብቱበትና ይደበድቡት ነበር፤
63Jėzų saugantys vyrai tyčiojosi iš Jo ir mušė.
64ሸፍነውም ፊቱን ይመቱት ነበርና። በጥፊ የመታህ ማን ነው? ትንቢት ተናገር እያሉ ይጠይቁት ነበር።
64Uždengę akis, jie daužė Jam per veidą ir klausinėjo: “Pranašauk, kas Tave užgavo!”
65ሌላም ብዙ ነገር እየተሳደቡ በእርሱ ላይ ይናገሩ ነበር።
65Ir visaip kitaip jam piktžodžiavo.
66በነጋም ጊዜ የሕዝቡ ሽማግሌዎችና የካህናት አለቆች ጻፎችም ተሰብስበው ወደ ሸንጎአቸው ወሰዱትና
66Rytui išaušus, susirinko tautos vyresnieji, aukštieji kunigai ir Rašto žinovai. Jie atvedė Jėzų į savo sinedrioną ir sakė:
67ክርስቶስ አንተ ነህን? ንገረን አሉት። እርሱ ግን እንዲህ አላቸው። ብነግራችሁ አታምኑም፤
67“Jei Tu Kristus, tai prisipažink mums!” Jėzus atsiliepė: “Jeigu jums ir pasakysiu, vis tiek netikėsite,
68ብጠይቅም አትመልሱልኝም አትፈቱኝምም።
68o jei paklausiu, man neatsakysite ir nepaleisite.
69ነገር ግን ከአሁን ጀምሮ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ኃይል ቀኝ ይቀመጣል።
69Tačiau nuo šio meto Žmogaus Sūnus sėdės Dievo Galybės dešinėje”.
70ሁላቸውም። እንግዲያስ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህን? አሉት። እርሱም። እኔ እንደ ሆንሁ እናንተ ትላላችሁ አላቸው።
70Tuomet jie visi klausė: “Tai Tu esi Dievo Sūnus?” Jis atsakė: “Taip yra kaip sakote: Aš Esu!”
71እነርሱም። ራሳችን ከአፉ ሰምተናልና ከእንግዲህ ወዲህ ምን ምስክር ያስፈልገናል? አሉ።
71Tada jie tarė: “Kam dar mums liudijimas?! Juk mes girdėjome iš Jo paties lūpų!”