1Prisiartinęs prie Jeruzalės pro Betfagę ir Betaniją, ties Alyvų kalnu, Jėzus pasiuntė du savo mokinius,
1ወደ ኢየሩሳሌምም ከደብረ ዘይት አጠገብ ወዳሉቱ ወደ ቤተ ፋጌና ወደ ቢታንያ በቀረቡ ጊዜ፥ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ልኮ።
2liepdamas: “Eikite į priešais esantį kaimą ir, vos įžengę į jį, rasite pririštą asilaitį, kuriuo dar niekas iš žmonių nėra jojęs. Atriškite jį ir atveskite”.
2በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ፥ ወዲያውም ወደ እርስዋ ገብታችሁ ከሰው ማንም ገና ያልተቀመጠበት ውርንጫ ታስሮ ታገኛላችሁ፤ ፈትታችሁ አምጡልኝ።
3Jeigu kas nors paklaustų: ‘Ką čia darote?’, atsakykite: ‘Jo reikia Viešpačiui’, ir iš karto jį paleis.
3ማንም። ስለ ምን እንዲህ ታደርጋላችሁ? ቢላችሁ። ለጌታ ያስፈልገዋል በሉት፥ ወዲያውም ደግሞ ወደዚህ ይሰደዋል አላቸው።
4Nuėję jiedu rado pakelėje asilaitį, pririštą prie vartų, ir atrišo jį.
4ሄዱም ውርንጫውንም በመንገድ መተላለፊያ በደጅ ውጭ ታስሮ አገኙት፥ ፈቱትም።
5Kai kurie iš ten stovinčių jų paklausė: “Ką darote, kam atrišate asilaitį?”
5በዚያም ከቆሙት አንዳንዶቹ። ውርንጫውን የምትፈቱት ምን ልታደርጉት ነው አሉአቸው።
6O jie atsakė taip, kaip Jėzus buvo jiems liepęs, ir tie leido jį vestis.
6እነርሱም ኢየሱስ እንዳዘዘ አሉአቸው፤ ተዉአቸውም።
7Jie atvedė asilaitį pas Jėzų, apdengė jį savo apsiaustais, ir Jėzus užsėdo ant jo.
7ውርንጫውንም ወደ ኢየሱስ አመጡት፥ ልብሳቸውንም በላዩ ጣሉ፥ ተቀመጠበትም።
8Daugelis tiesė ant kelio savo drabužius, kiti kirto ir klojo ant kelio medžių šakas.
8ብዙ ሰዎችም ልብሳቸውን በመንገድ ላይ አነጠፉ፥ ሌሎችም ከዛፍ ቅጠሎችን እየቈረጡ ያነጥፉ ነበር።
9Iš priekio ir iš paskos einantys šaukė: “Osana! Palaimintas, kuris ateina Viešpaties vardu!
9የሚቀድሙትም የሚከተሉትም። ሆሣዕና፤ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤
10Palaiminta mūsų tėvo Dovydo karalystė, ateinanti Viešpaties vardu! Osana aukštybėse!”
10በጌታ ስም የምትመጣ የአባታችን የዳዊት መንግሥት የተባረከች ናት፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር።
11Taip Jėzus įžengė į Jeruzalę ir į šventyklą. Viską apžiūrėjęs, kadangi buvo jau vakaro valanda,Jis su dvylika išėjo į Betaniją.
11ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወደ መቅደስ ገባ፤ ዘወር ብሎም ሁሉን ከተመለከተ በኋላ፥ ጊዜው መሽቶ ስለ ነበረ ከአሥራ ሁለቱ ጋር ወደ ቢታንያ ወጣ።
12Rytojaus dieną, jiems keliaujant iš Betanijos, Jėzus išalko.
12በማግሥቱም ከቢታንያ ሲወጡ ተራበ።
13Pamatęs iš tolo sulapojusį figmedį, Jis priėjo pažiūrėti, gal ką ant jo ras. Tačiau, atėjęs prie medžio, Jis nerado nieko, tiktai lapus, nes dar nebuvo figų metas.
13ቅጠልም ያላት በለስ ከሩቅ አይቶ ምናልባት አንዳች ይገኝባት እንደ ሆነ ብሎ መጣ፥ ነገር ግን የበለስ ወራት አልነበረምና መጥቶ ከቅጠል በቀር ምንም አላገኘባትም።
14Atsakydamas Jėzus tarė medžiui: “Tegul per amžius niekas nebevalgys tavo vaisiaus!” Jo mokiniai tai girdėjo.
14መልሶም። ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም ማንም ከአንቺ ፍሬ አይብላ አላት። ደቀ መዛሙርቱም ሰሙ።
15Jie atėjo į Jeruzalę. Įėjęs į šventyklą, Jėzus ėmė varyti laukan parduodančius ir perkančius šventykloje. Jis išvartė pinigų keitėjų stalus bei karvelių pardavėjų suolus
15ወደ ኢየሩሳሌምም መጡ። ወደ መቅደስም ገብቶ በመቅደስ የሚሸጡትንና የሚገዙትን ያወጣ ጀመር፥ የገንዘብ ለዋጮችንም ገበታዎች የርግብ ሻጭዎችንም ወንበሮች ገለበጠ፤
16ir neleido nešti prekių per šventyklą.
16ዕቃም ተሸክሞ ማንም በመቅደስ ሊያልፍ አልፈቀደም።
17Jis mokė, sakydamas jiems: “Argi neparašyta: ‘Mano namai vadinsis maldos namai visoms tautoms’? O jūs pavertėte juos ‘plėšikų lindyne’ ”.
17አስተማራቸውም። ቤቴ ለአሕዛብ ሁሉ የጸሎት ቤት ትባላለች ተብሎ የተጻፈ አይደለምን? እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት አላቸው።
18Tai išgirdę, aukštieji kunigai ir Rašto žinovai tarėsi, kaip Jį pražudyti. Jie mat bijojo Jėzaus, nes visi žmonės buvo didžiai nustebinti Jo mokymo.
18የካህናት አለቆችም ጻፎችም ሰምተው፥ ሕዝቡ ሁሉ በትምህርቱ ይገረሙ ስለ ነበር ይፈሩት ነበርና እንዴት አድርገው እንዲያጠፉት ፈለጉ።
19Atėjus vakarui, Jėzus su mokiniais išėjo iš miesto.
19ማታ ማታም ከከተማ ወደ ውጭ ይወጣ ነበር።
20Rytą eidami pro šalį, jie pamatė, kad figmedis nudžiūvęs iš pat šaknų.
20ማለዳም ሲያልፉ በለሲቱን ከሥርዋ ደርቃ አዩአት።
21Prisiminęs Petras tarė Jėzui: “Rabi, žiūrėk! Figmedis, kurį prakeikei, nudžiūvo!”
21ጴጥሮስም ትዝ ብሎት። መምህር ሆይ፥ እነሆ፥ የረገምሃት በለስ ደርቃለች አለው።
22Jėzus, atsakydamas jiems, tarė: “Turėkite tikėjimą Dievu!
22ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። በእግዚአብሔር እመኑ።
23Iš tiesų sakau jums: kas pasakytų šitam kalnui: ‘Pasikelk ir meskis į jūrą’, ir savo širdyje neabejotų, bet tikėtų, kad įvyks tai, ką sako,jis turės, ką besakytų.
23እውነት እላችኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ ይህን ተራራ። ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል።
24Todėl sakau jums: ko tik prašote melsdamiesi, tikėkite, kad gaunate, ir jūs turėsite.
24ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል።
25Kai stovite melsdamiesi, atleiskite, jei turite ką nors prieš kitus, kad ir jūsų Tėvas, kuris danguje, galėtų jums atleisti jūsų nusižengimus.
25ለጸሎትም በቆማችሁ ጊዜ፥ በሰማያት ያለው አባታችሁ ደግሞ ኃጢአታችሁን ይቅር እንዲላችሁ፥ በማንም ላይ አንዳች ቢኖርባችሁ ይቅር በሉት።
26Bet jeigu jūs neatleisite, nė jūsų Tėvas, kuris danguje, neatleis jūsų nusižengimų”.
26እናንተ ግን ይቅር ባትሉ በሰማያት ያለው አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።
27Jie vėl sugrįžo į Jeruzalę. Jam vaikščiojant po šventyklą, prie Jo priėjo aukštųjų kunigų, Rašto žinovų bei vyresniųjų
27ደግሞም ወደ ኢየሩሳሌም መጡ። እርሱም በመቅደስ ሲመላለስ፥ የካህናት አለቆችና ጻፎች ሽማግሌዎችም ወደ እርሱ መጥተው።
28ir klausė: “Kokią teisę turi taip daryti? Kas Tau davė valdžią tai daryti?”
28እነዚህን በምን ሥልጣን ታደርጋለህ? ወይስ እነዚህን ለማድረግ ይህን ሥልጣን ማን ሰጠህ? አሉት።
29Jėzus jiems atsakė: “Aš irgi paklausiu jus vieno dalyko, o jūs atsakykite man, tada ir Aš jums pasakysiu, kokia valdžia tai darau.
29ኢየሱስም። እኔም አንዲት ነገር እጠይቃችኋለሁ፥ እናንተም መልሱልኝ፥ እኔም በምን ሥልጣን እነዚህን እንዳደርግ እነግራችኋለሁ።
30Jono krikštas buvo iš dangaus ar iš žmonių? Atsakykite man!”
30የዮሐንስ ጥምቀት ከሰማይ ነበረችን ወይስ ከሰው? መልሱልኝ አላቸው።
31Jie samprotavo tarpusavy: “Jei pasakysimeiš dangaus, Jis mums sakys: ‘Tai kodėl juo netikėjote?’
31እርስ በርሳቸውም ሲነጋገሩ። ከሰማይ ነው ብንል። እንግዲያውስ ስለ ምን አላመናችሁበትም? ይለናል፤
32O jei pasakysimeiš žmonių...” Jie bijojo minios, nes visi buvo įsitikinę, kad Jonas tikrai buvo pranašas.
32ነገር ግን። ከሰው ነው እንበልን? አሉ፤ ሁሉ ዮሐንስን በእውነት እንደ ነቢይ ያዩት ነበርና ሕዝቡን ፈሩ።
33Todėl jie atsakė Jėzui: “Mes nežinome”. Tada Jėzus tarė: “Tai ir Aš jums nesakysiu, kokia valdžia tai darau”.
33ለኢየሱስም መልሰው። አናውቅም አሉት ኢየሱስም። እኔም በምን ሥልጣን እነዚህን እንዳደርግ አልነግራችሁም አላቸው።