Lithuanian

Amharic: New Testament

Mark

13

1Jam išeinant iš šventyklos, vienas iš mokinių Jam sako: “Mokytojau, pažvelk, kokie akmenys ir kokie pastatai!”
1እርሱም ከመቅደስ ሲወጣ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ። መምህር ሆይ፥ እንዴት ያሉ ድንጋይዎችና እንዴት ያሉ ሕንጻዎች እንደ ሆኑ እይ አለው።
2Jėzus jam atsakė: “Matai šituos didžiulius pastatus? Čia neliks akmens ant akmens, viskas bus išgriauta”.
2ኢየሱስም መልሶ። እነዚህን ታላላቅ ሕንጻዎች ታያለህን? ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አለው።
3Kai Jis sėdėjo Alyvų kalne, priešais šventyklą, Petras, Jokūbas, Jonas ir Andriejus atskirai nuo kitų klausė Jį:
3በመቅደስም ትይዩ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ጴጥሮስና ያዕቆብ ዮሐንስም እንድርያስም።
4“Pasakyk mums, kada tai įvyks ir koks bus ženklas, kai visa tai pradės pildytis?”
4ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? ይህስ ሁሉ ይፈጸም ዘንድ እንዳለው ምልክቱ ምንድር ነው? ብለው ለብቻቸው ጠየቁት።
5Jėzus, jiems atsakydamas, pradėjo kalbėti: “Žiūrėkite, kad niekas jūsų nesuklaidintų.
5ኢየሱስም መልሶ እንዲህ ይላቸው ጀመር። ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ።
6Daug kas ateis mano vardu ir sakys: ‘Tai Aš’, ir daugelį suklaidins.
6ብዙዎች። እኔ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፥ ብዙዎችንም ያስታሉ።
7Išgirdę apie karus ir karų gandus, neišsigąskite. Tai turi įvykti, bet dar ne galas.
7ጦርንም የጦርንም ወሬ በሰማችሁ ጊዜ አትደንግጡ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና፥ ነገር ግን መጨረሻው ገና ነው።
8Tauta sukils prieš tautą ir karalystė prieš karalystę. Įvairiose vietose bus žemės drebėjimų, bus badmečių ir neramumų. Tai gimdymo skausmų pradžia.
8ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፤ በልዩ ልዩ ስፍራ የምድር መናወጥ ይሆናል፤ ራብ ይሆናል፤ እነዚህ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።
9Jūs saugokitės, nes atidavinės jus teismams, plaks sinagogose, ir jūs turėsite dėl manęs stoti prieš valdytojus ir karalius jiems liudyti.
9እናንተ ግን ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤ ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል በምኵራብም ትገረፋላችሁ ምስክርም ይሆንባቸው ዘንድ ስለ እኔ በገዥዎችና በነገሥታት ፊት ትቆማላችሁ።
10Ir Evangelija pirmiau turės būti paskelbta visoms tautoms.
10አስቀድሞም ወንጌል ለአሕዛብ ሁሉ ይሰበክ ዘንድ ይገባል።
11Kai suėmę jus ves, nesirūpinkite ir negalvokite iš anksto, ką kalbėsite. Kalbėkite tai, kas tą valandą bus jums duota, nes kalbėsite ne jūs, o Šventoji Dvasia.
11ሲጐትቱአችሁና አሳልፈው ሲሰጡአችሁም ምን እንድትናገሩ አስቀድማችሁ አትጨነቁ፥ ዳሩ ግን በዚያች ሰዓት የሚሰጣችሁን ተናገሩ፤ የሚነግረው መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እናንተ አይደላችሁምና።
12Brolis išduos nužudyti brolį, o tėvas­savo vaiką. Vaikai pakels ranką prieš savo gimdytojus ir juos žudys.
12ወንድምም ወንድሙን አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ። ይገድሉአቸውማል፤
13Jūs būsite visų nekenčiami dėl mano vardo. Bet kas ištvers iki galo, tas bus išgelbėtas”.
13በሁሉም ዘንድ ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል።
14“Kai pamatysite per pranašą Danielių paskelbtą naikinimo bjaurastį, stovinčią ten, kur jos neturi būti (kas skaito­teišmano), tada, kas bus Judėjoje, tebėga į kalnus;
14ነገር ግን በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋት ርኵሰት በማይገባው ስፍራ ቆሞ ብታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥ በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፥
15kas bus ant stogo, tenelipa žemyn į namus ir tegul neina ko nors pasiimti iš savo namų;
15በሰገነትም ያለ ወደ ቤት አይውረድ ከቤቱም አንዳች ይወስድ ዘንድ አይግባ፥
16o kas laukuose, tenegrįžta pasiimti apsiausto.
16በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ።
17Vargas nėščioms ir žindančioms tomis dienomis!
17በዚያን ወራትም ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው።
18Melskitės, kad jums netektų bėgti žiemą!
18ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ፤
19Tomis dienomis bus toks suspaudimas, kokio nėra buvę nuo pradžios pasaulio, kurį Dievas sutvėrė, iki šiol, ir daugiau nebebus.
19በዚያን ወራት እግዚአብሔር ከፈጠረው ከፍጥረት መጀመሪያ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያልሆነ ደግሞም የማይሆን የመከራ ዓይነት ይሆናልና።
20Ir, jeigu Viešpats nebūtų sutrumpinęs tų dienų, neišsigelbėtų nė vienas kūnas. Tačiau dėl išrinktųjų, kuriuos išsirinko, Jis sutrumpino tas dienas.
20ጌታስ ወራቶቹን ባያሳጥር፥ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም፤ ነገር ግን ስለ መረጣቸው ምርጦች ወራቶቹን አሳጠረ።
21Jei tada kas nors jums sakys: ‘Štai čia Kristus’, arba: ‘Jis tenai!’,­netikėkite,
21በዚያን ጊዜም ማንም። እነሆ፥ ክርስቶስ ከዚህ አለ፥ ወይም። እነሆ፥ ከዚያ አለ ቢላችሁ አትመኑ፤
22nes atsiras netikrų kristų ir netikrų pranašų. Jie darys ženklų ir stebuklų, kad suklaidintų, jei įmanoma, net išrinktuosius.
22ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ ያስቱ ዘንድ ምልክትና ድንቅ ያደርጋሉ።
23Todėl būkite atidūs; štai Aš jums iš anksto visa tai pasakiau”.
23እናንተ ግን ተጠንቀቁ፤ እነሆ፥ አስቀድሜ ሁሉን ነገርኋችሁ።
24“Tomis dienomis, po ano suspaudimo, saulė užtems, mėnulis nebeduos šviesos,
24በዚያን ወራት ግን ከዚያ መከራ በኋላ ፀሐይ ይጨልማል ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፥
25dangaus žvaigždės kris ir dangaus jėgos bus sudrebintos.
25ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፥ የሰማያትም ኃይላት ይናወጣሉ።
26Tada jie pamatys Žmogaus Sūnų, ateinantį debesyse su didžia jėga ir šlove.
26በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በብዙ ኃይልና ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል።
27Jis pasiųs savo angelus, ir tie surinks Jo išrinktuosius iš keturių žemės pusių, nuo žemės pakraščių iki dangaus tolybių.
27በዚያን ጊዜም መላእክትን ይልካል ከአራቱ ነፋሳትም ከምድር ዳርቻ እስከ ሰማይ ዳርቻ የተመረጡትን ይሰበስባቸዋል።
28Pasimokykite iš palyginimo su figmedžiu: kai jo šaka suminkštėja ir sprogsta lapai, žinote, jog artėja vasara.
28ምሳሌውንም ከበለስ ተማሩ፤ ጫፍዋ ሲለሰልስ ቅጠልዋም ሲያቈጠቍጥ፥ ያን ጊዜ በጋ እንደ ቀረበ ታውቃላችሁ፤
29Taip pat jūs, išvydę visa tai dedantis, žinokite, jog Jis jau arti, prie durų.
29እንዲሁ ደግሞ እናንተ ይህን ሁሉ መሆኑን ስታዩ ቀርቦ በደጅ እንደ ሆነ እወቁ።
30Iš tiesų sakau jums: ši karta nepraeis, iki visa tai įvyks.
30እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም።
31Dangus ir žemė praeis, o mano žodžiai nepraeis.
31ሰማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን አያልፍም።
32Tačiau tos dienos ir valandos niekas nežino, nei angelai danguje, nei Sūnus, tik Tėvas”.
32ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን ከአባት በቀር የሚያውቅ የለም።
33“Žiūrėkite, budėkite ir melskitės, nes nežinote, kada ateis laikas!
33ጊዜው መቼ እንዲሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፤ ጸልዩም።
34Bus kaip su žmogumi, kuris iškeliavo toli, paliko namus, suteikė tarnams valdžią, kiekvienam paskyrė darbą, o durininkui įsakė budėti.
34ቤቱን ትቶ ወደ ሌላ አገር እንደ ሄደ ሰው ነው፥ ለባሮቹም ሥልጣን ለእያንዳንዱም ሥራውን ሰጥቶ በረኛውን እንዲተጋ አዘዘ።
35Taigi budėkite, nes nežinote, kada grįš namų šeimininkas: ar vakare, ar vidurnaktyje, ar gaidžiui giedant, ar rytmety,
35እንግዲህ በማታ ቢሆን ወይም በእኩለ ሌሊት ወይም ዶሮ ሲጮኽ ወይም በማለዳ ቢሆን ባለቤቱ መቼ እንዲመጣ አታውቁምና
36kad, netikėtai sugrįžęs, nerastų jūsų miegančių.
36ድንገት መጥቶ ተኝታችሁ እንዳያገኛችሁ ስለዚህ ትጉ።
37Ką sakau jums, sakau ir visiems: budėkite!”
37ለእናንተም የምነግራችሁ ለሁሉ እላለሁ፤ ትጉ።