Lithuanian

Amharic: New Testament

Mark

14

1Iki Paschos ir Neraugintos duonos šventės buvo likę dvi dienos. Aukštieji kunigai ir Rašto žinovai ieškojo būdo klasta suimti Jėzų ir nužudyti.
1ከሁለት ቀን በኋላ ፋሲካና የቂጣ በዓል ነበረ። የካህናት አለቆችም ጻፎችም እንዴት አድርገው በተንኰል እንደሚይዙትና እንደሚገድሉት ይፈልጉ ነበር።
2Bet jie sakė: “Tik ne per šventes, kad žmonėse nekiltų sąmyšio”.
2የሕዝብ ሁከት እንዳይሆን በበዓል አይሁን ይሉ ነበርና።
3Jėzui esant Betanijoje, Simono Raupsuotojo namuose, ir sėdint prie stalo, atėjo moteris su alebastriniu labai brangaus gryno nardo tepalo indu. Sudaužiusi indą, ji išpylė tepalą Jam ant galvos.
3እርሱም በቢታንያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት በነበረ ጊዜ፥ በማዕድ ተቀምጦ ሳለ፥ አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የከበረ ጥሩ ናርዶስ ሽቱ የመላበት የአልባስጥሮስ ቢልቃጥ ይዛ መጣች፤ ቢልቃጡንም ሰብራ በራሱ ላይ አፈሰሰችው።
4Kai kurie ten esantys pasipiktino ir kalbėjo vienas kitam: “Kam toks tepalo eikvojimas?
4አንዳንዶችም። ይህ የሽቱ ጥፋት ለምንድር ነው?
5Juk jį buvo galima parduoti daugiau negu už tris šimtus denarų ir pinigus išdalyti vargšams!” Ir jie murmėjo prieš tą moterį.
5ይህ ሽቱ ከሦስት መቶ ዲናር በሚበልጥ ዋጋ ተሽጦ ለድሆች ሊሰጥ ይቻል ነበርና ብለው በራሳቸው ይቈጡ ነበር፤ እርስዋንም ነቀፉአት።
6Bet Jėzus atsiliepė: “Palikite ją ramybėje! Kam ją skaudinate? Ji man padarė gerą darbą.
6ኢየሱስ ግን እንዲህ አለ። ተዉአት፤ ስለ ምን ታደክሙአታላችሁ? መልካም ሥራ ሠርታልኛለች።
7Vargšų jūs visuomet turite su savimi ir, kada tik panorėję, galėsite jiems gera daryti, o mane ne visuomet turėsite.
7ድሆች ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና፥ በማናቸውም በወደዳችሁት ጊዜ መልካም ልታደርጉላቸው ትችላላችሁ፥ እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም።
8Ji padarė, ką galėjo. Ji iš anksto patepė mano kūną laidotuvėms.
8የተቻላትን አደረገች፤ አስቀድማ ለመቃብሬ ሥጋዬን ቀባችው።
9Iš tiesų sakau jums: visame pasaulyje, kur tik bus skelbiama ši Evangelija, jos atminimui bus pasakojama ir tai, ką ji padarė”.
9እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለሙ ሁሉ በሚሰበክበት በማናቸውም ስፍራ፥ እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ ሊሆን ይነገራል።
10Judas Iskarijotas, vienas iš dvylikos, nuėjo pas aukštuosius kunigus išduoti Jėzų.
10ከአሥራ ሁለቱም አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ ሊሰጠው ወደ ካህናት አለቆች ሄደ።
11Tai išgirdę, jie apsidžiaugė ir pažadėjo jam pinigų. Jis ėmė ieškoti progos Jėzų išduoti.
11ሲሰሙም ደስ አላቸው ብርም ይሰጡት ዘንድ ተስፋ ሰጡት። በሚመች ጊዜም እንዴት አድርጎ አሳልፎ እንዲሰጠው ይፈልግ ነበር።
12Pirmąją Neraugintos duonos dieną, kada pjaunamas Paschos avinėlis, mokiniai klausė Jėzų: “Kur nori, kad Tau paruoštume valgyti Paschą?”
12ፋሲካን በሚያርዱበት በቂጣ በዓል መጀመሪያ ቀን ደቀ መዛሙርቱ። ፋሲካን ትበላ ዘንድ ወዴት ሄደን ልናሰናዳ ትወዳለህ? አሉት።
13Jis pasiunčia du mokinius, tardamas: “Eikite į miestą. Ten jus sutiks žmogus, vandens ąsočiu nešinas. Sekite paskui jį
13ከደቀ መዛሙርቱም ሁለት ላከ እንዲህም አላቸው። ወደ ከተማ ሂዱ፥ ማድጋ ውኃ የተሸከመ ሰውም ይገናኛችኋል፤
14ir, kur jis įeis, sakykite namų šeimininkui: ‘Mokytojas liepė paklausti: kur yra svečių kambarys, kuriame su savo mokiniais galėčiau valgyti Paschą?’
14ተከተሉት፥ የሚገባበትንም የቤቱን ጌታ። መምህሩ። ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ፋሲካን የምበላበት የእንግዳ ቤት ወዴት ነው? ይላል በሉት።
15Jis parodys jums didelį apstatytą aukštutinį kambarį. Ten ir paruoškite mums”.
15እርሱም በደርብ ላይ ያለውን የተሰናዳና የተነጠፈ ታላቅ አዳራሽ ያሳያችኋል፤
16Mokiniai išėjo ir nuvyko į miestą. Jie rado visa, kaip Jis sakė, ir paruošė Paschą.
16በዚያም አሰናዱልን። ደቀ መዛሙርቱም ወጡ ወደ ከተማም ሄደው እንዳላቸው አገኙ፥ ፋሲካንም አሰናዱ።
17Vakare Jis atėjo su dvylika.
17በመሸም ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ጋር መጣ።
18Jiems sėdint už stalo ir valgant, Jėzus tarė: “Iš tiesų sakau jums: vienas iš jūsų, valgančių su manimi, išduos mane”.
18ተቀምጠውም ሲበሉ ኢየሱስ። እውነት እላችኋለሁ፥ ከእናንተ አንዱ፥ እርሱም ከእኔ ጋር የሚበላው አሳልፎ ይሰጠኛል አለ።
19Jie labai nuliūdo ir vienas paskui kitą ėmė Jo klausinėti: “Nejaugi aš?”, “Nejaugi aš?”
19እነርሱም ያዝኑ፥ እያንዳንዳቸውም። እኔ እሆንን? ይሉት ጀመር።
20O Jis jiems tarė: “Vienas iš dvylikos, kuris dažo su manimi dubenyje.
20እርሱም መልሶ። ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ከእኔ ጋር ወደ ወጭቱ እጁን የሚያጠልቀው ነው።
21Žmogaus Sūnus, tiesa, eina, kaip apie Jį parašyta, bet vargas tam žmogui, per kurį Žmogaus Sūnus išduodamas. Geriau būtų buvę tam žmogui negimti”.
21የሰው ልጅስ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈ ይሄዳል፤ ነገር ግን የሰው ልጅ አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት፤ ያ ሰው ባልተወለደ ይሻለው ነበር አላቸው።
22Jiems bevalgant, Jėzus paėmė duoną, palaimino, laužė ir davė mokiniams, sakydamas: “Imkite ir valgykite: tai yra mano kūnas!”
22ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ሰጣቸውና። እንካችሁ፤ ይህ ሥጋዬ ነው አለ።
23Po to paėmė taurę, padėkojo, davė jiems, ir visi gėrė iš jos.
23ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው፥ ሁሉም ከእርሱ ጠጡ።
24Jis jiems tarė: “Tai yra mano kraujas, Naujosios Sandoros kraujas, kuris išliejamas už daugelį.
24እርሱም። ይህ ስለ ብዙዎች የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ነው።
25Iš tiesų sakau jums: Aš daugiau nebegersiu vynmedžio vaisiaus iki tos dienos, kada gersiu jį naują Dievo karalystėje”.
25እውነት እላችኋለሁ፥ በእግዚአብሔር መንግሥት ከወይኑ ፍሬ አዲሱን እስከምጠጣበት እስከዚያ ቀን ድረስ ደግሞ አልጠጣውም አላቸው።
26Pagiedoję himną, jie išėjo į Alyvų kalną.
26መዝሙርም ከዘመሩ በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ወጡ።
27Jėzus jiems tarė: “Šią naktį jūs visi manimi pasipiktinsite, nes parašyta: ‘Ištiksiu piemenį, ir avys išsisklaidys’.
27ኢየሱስም። በዚች ሌሊት ሁላችሁ በእኔ ትሰናከላላችሁ፤ እረኛዉን እመታለሁ በጎችም ይበተናሉ የሚል ተጽፎአልና።
28Bet prisikėlęs Aš pirma jūsų nueisiu į Galilėją”.
28ነገር ግን ከተነሣሁ በኋላ ወደ ገሊላ እቀድማችኋለሁ አላቸው።
29Petras atsiliepė: “Jei ir visi pasipiktintų, tai tik ne aš!”
29ጴጥሮስም። ሁሉም ቢሰናከሉ እኔ ግን ከቶ አልሰናከልም አለው።
30Jėzus jam atsakė: “Iš tiesų sakau tau: dar šiandien, jau šią naktį, gaidžiui nė dukart nepragydus, tu tris kartus manęs išsiginsi”.
30ኢየሱስም። እውነት እልሃለሁ፥ ዛሬ በዚች ሌሊት ዶሮ ሁለት ጊዜ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ አለው።
31Bet Petras dar atkakliau tvirtino: “Jei man reikėtų net mirti su Tavimi, aš vis tiek Tavęs neišsiginsiu”. Tą patį kalbėjo ir visi kiti.
31እርሱም ቃሉን አበርትቶ። ከአንተ ጋር የምሞት እንኳ ቢሆን ከቶ አልክድህም አለ። ሁሉም ደግሞ እንደዚሁ አሉ።
32Jie atėjo į vietą, vadinamą Getsemane. Jėzus sako savo mokiniams: “Pasėdėkite čia, kol Aš melsiuosi”.
32ጌቴሴማኒ ወደምትባልም ስፍራ መጡ፥ ደቀ መዛሙርቱንም። ስጸልይ ሳለሁ፥ በዚህ ተቀመጡ አላቸው።
33Pasiėmęs su savimi Petrą, Jokūbą ir Joną, Jis pradėjo nuogąstauti ir sielvartauti.
33ጴጥሮስንና ያዕቆብን ዮሐንስንም ከእርሱ ጋር ወሰደ፤ ሊደነግጥም ሊተክዝም ጀመረና።
34Jis jiems sakė: “Mano siela mirtinai nuliūdusi. Pasilikite čia ir budėkite!”
34ነፍሴ እስከ ሞት ድረስ እጅግ አዘነች፤ በዚህ ቈዩ ትጉም አላቸው።
35Paėjęs truputį toliau, sukniubo ant žemės ir meldėsi, kad, jei įmanoma, Jį aplenktų toji valanda.
35ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በምድርም ወድቆ፥ ይቻልስ ቢሆን ሰዓቲቱ ከእርሱ እንድታልፍ ጸለየና።
36Jis sakė: “Aba, Tėve, Tau viskas įmanoma. Atitolink nuo manęs šitą taurę! Tačiau ne kaip Aš noriu, bet kaip Tu”.
36አባ አባት ሆይ፥ ሁሉ ይቻልሃል፤ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን አንተ የምትወደው እንጂ እኔ የምወደው አይሁን አለ።
37Po to grįžta, randa juos miegančius ir taria Petrui: “Simonai, tu miegi? Nepajėgei nė vienos valandos pabudėti?
37መጣም ተኝተውም አገኛቸው፥ ጴጥሮስንም። ስምዖን ሆይ፥ ተኝተሃልን? አንዲት ሰዓት ስንኳ ልትተጋ አልቻልህምን?
38Budėkite ir melskitės, kad nepatektumėte į pagundymą, nes dvasia ryžtinga, bet kūnas silpnas”.
38ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉ ጸልዩም፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች፥ ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።
39Jis vėl nuėjo ir meldėsi tais pačiais žodžiais.
39ደግሞም ሄዶ ያንኑ ቃል ጸለየ።
40Sugrįžęs Jis vėl rado juos miegančius­jų akys buvo apsunkusios, ir jie nežinojo, ką atsakyti.
40ደግሞም መጥቶ ዓይኖቻቸው በእንቅልፍ ከብደው ነበርና ተኝተው አገኛቸው፥ የሚመልሱለትንም አላወቁም።
41Jis atėjo trečią kartą ir tarė jiems: “Vis dar tebemiegate ir ilsitės? Gana! Atėjo valanda: štai Žmogaus Sūnus išduodamas į nusidėjėlių rankas.
41ሦስተኛም መጥቶ። እንግዲህስ ተኙ ዕረፉም፤ ይበቃል፤ ሰዓቲቱ ደረሰች፤ እነሆ፥ የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ይሰጣል።
42Kelkitės, eime! Štai mano išdavėjas čia pat”.
42ተነሡ፥ እንሂድ፤ እነሆ፥ አሳልፎ የሚሰጠኝ ቀርቦአል አላቸው።
43Ir tuojau, dar Jam tebekalbant, pasirodė vienas iš dvylikos­Judas, o kartu su juo didelė minia, ginkluota kalavijais ir vėzdais, pasiųsta aukštųjų kunigų, Rašto žinovų ir vyresniųjų.
43ወዲያውም ገና ሲናገር ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ይሁዳ መጣ፥ ከእርሱም ጋር ብዙ ሰዎች ሰይፍና ጐመድ ይዘው ከካህናት አለቆችና ከጻፎች ከሽማግሌዎችም ዘንድ መጡ።
44Išdavėjas buvo jiems nurodęs ženklą: “Kurį pabučiuosiu, tai Tas. Suimkite Jį ir veskite saugodami!”
44አሳልፎ የሚሰጠውም። የምስመው እርሱ ነው፤ ያዙት ተጠንቅቃችሁም ውሰዱት ብሎ ምልክት ሰጥቶአቸው ነበር።
45Atėjęs jis tuojau prisiartino prie Jėzaus ir tarė: “Rabi!”, ir pabučiavo Jį.
45መጥቶም ወዲያው ወደ እርሱ ቀረበና። መምህር ሆይ፥ መምህር ሆይ፥ ብሎ ሳመው፤
46O kiti čiupo Jėzų rankomis ir suėmė.
46እነርሱም እጃቸውን በእርሱ ላይ ጭነው ያዙት።
47Vienas iš ten stovinčiųjų, išsitraukęs kalaviją, smogė vyriausiojo kunigo tarnui ir nukirto jam ausį.
47በአጠገብ ከቆሙት ግን አንዱ ሰይፉን መዞ የሊቀ ካህናቱን ባሪያ መታ ጆሮውንም ቈረጠ።
48O Jėzus jiems tarė: “Kaip prieš plėšiką išėjote su kalavijais ir vėzdais suimti manęs.
48ኢየሱስም መልሶ። ወንበዴ እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ልትይዙኝ መጣችሁን?
49Aš kasdien buvau su jumis šventykloje ir mokiau, ir jūs manęs nesuėmėte. Tačiau turi išsipildyti Raštai”.
49በመቅደስ ዕለት ዕለት እያስተማርሁ ከእናንተ ጋር ስኖር አልያዛችሁኝም፤ ነገር ግን መጻሕፍት ይፈጸሙ ዘንድ ይህ ሆነ አላቸው።
50Tada visi paliko Jį ir pabėgo.
50ሁሉም ትተውት ሸሹ።
51Vienas jaunuolis sekė Jį iš paskos, susisupęs vien į drobulę. Jie čiupo jį,
51ዕርቃኑን በነጠላ የሸፈነ አንድ ጎበዝ ይከተለው ነበር፥
52bet šis išsinėrė iš drobulės ir nuogas pabėgo.
52ጎበዛዝቱም ያዙት፤ እርሱ ግን ነጠላውን ትቶ ዕራቁቱን ሸሸ።
53Jėzų nuvedė pas vyriausiąjį kunigą, kur buvo susirinkę visi aukštieji kunigai, vyresnieji ir Rašto žinovai.
53ኢየሱስንም ወደ ሊቀ ካህናቱ ወሰዱት፥ የካህናት አለቆችም ሁሉ ሽማግሌዎችም ጻፎችም ተሰበሰቡ።
54Petras sekė Jį iš tolo iki vyriausiojo kunigo rūmų kiemo. Ten jis atsisėdo su tarnais ir šildėsi prie ugnies.
54ጴጥሮስም እስከ ሊቀ ካህናቱ ግቢ ውስጥ በሩቁ ተከተለው፥ ከሎሌዎችም ጋር ተቀምጦ እሳት ይሞቅ ነበር።
55Aukštieji kunigai ir visas sinedrionas ieškojo prieš Jėzų liudijimo, kad galėtų nuteisti Jį mirti, bet nerado.
55የካህናት አለቆችም ሸንጎውም ሁሉ እንዲገድሉት በኢየሱስ ላይ ምስክር ይፈልጉ ነበር፥ አላገኙምም፤
56Nors daugelis melagingai liudijo prieš Jį, tačiau jų liudijimai nesutapo.
56ብዙዎች በሐሰት ይመሰክሩበት ነበርና፥ ምስክርነታቸው ግን አልተሰማማም።
57Kai kurie atsistoję melagingai kaltino Jį, teigdami:
57ሰዎችም ተነሥተው። እኔ ይህን በእጅ የተሠራውን ቤተ መቅደስ አፈርሰዋለሁ በሦስት ቀንም ሌላውን በእጅ ያልተሠራውን እሠራለሁ ሲል ሰማነው ብለው በሐሰት መሰከሩበት።
58“Mes girdėjome Jį sakant: ‘Aš sugriausiu šitą rankomis pastatytą šventyklą ir per tris dienas pastatysiu kitą, ne rankų darbo’ ”.
59ምስክርነታቸውም እንዲሁ እንኳ አልተሰማማም።
59Bet ir šie kaltinimai nesutapo.
60ሊቀ ካህናቱም በመካከላቸው ተነሥቶ። አንዳች አትመልስምን? እነዚህስ በአንተ ላይ የሚመሰክሩብህ ምንድር ነው? ብሎ ኢየሱስን ጠየቀው።
60Tada vyriausiasis kunigas, atsistojęs viduryje, paklausė Jėzų: “Tu nieko neatsakai į šituos kaltinimus?”
61እርሱ ግን ዝም አለ አንዳችም አልመለሰም። ደግሞ ሊቀ ካህናቱ ጠየቀውና። የቡሩክ ልጅ ክርስቶስ አንተ ነህን? አለው።
61Tačiau Jis tylėjo ir nieko neatsakė. Tada vyriausiasis kunigas vėl Jį paklausė: “Ar Tu esi Kristus, Palaimintojo Sūnus?!”
62ኢየሱስም። እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅም በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ በሰማይም ደመና ሲመጣ ታያላችሁ አለ።
62Ir Jėzus pasakė: “Aš Esu. Ir jūs išvysite Žmogaus Sūnų, sėdintį Galybės dešinėje ir ateinantį dangaus debesyse”.
63ሊቀ ካህናቱም ልብሱን ቀደደና። ከእንግዲህ ወዲህ ምስክሮችን ምን ያስፈልገናል?
63Tada vyriausiasis kunigas persiplėšė drabužius ir sušuko: “Kam dar mums liudytojai?
64ስድቡን ሰማችሁ፤ ምን ይመስላችኋል? አለ። እነርሱም ሁሉ። ሞት ይገባዋል ብለው ፈረዱበት።
64Jūs girdėjote piktžodžiavimą! Kaip jums atrodo?” Ir jie visi nusprendė Jį esant vertą mirties.
65አንዳንዶችም ይተፉበት ፊቱንም ሸፍነው ይጐስሙትና። ትንቢት ተናገር ይሉት ጀመር፤ ሎሌዎችም በጥፊ እየመቱ ወሰዱት።
65Kai kurie pradėjo į Jį spjaudyti, dangstė Jam veidą, mušė kumščiais ir sakė: “Pranašauk!” O tarnai daužė Jį per veidą.
66ጴጥሮስም በግቢ ውስጥ ወደ ታች ሳለ ከሊቀ ካህናቱ ገረዶች አንዲቱ መጣች፥
66Petrui esant žemai, kieme, atėjo viena vyriausiojo kunigo tarnaitė
67ጴጥሮስም እሳት ሲሞቅ አይታ ተመለከተችውና። አንተ ደግሞ ከናዝሬቱ ከኢየሱስ ጋር ነበርህ አለችው።
67ir, pamačiusi besišildantį Petrą, įsižiūrėjo į jį ir tarė: “Ir tu buvai su šituo Nazariečiu Jėzumi”.
68እርሱ ግን። የምትዪውን አላውቅም አላስተውልምም ብሎ ካደ። ወደ ውጭም ወደ ደጅ ወጣ፤ ዶሮም ጮኸ።
68Bet Petras išsigynė, sakydamas: “Nei žinau, nei suprantu, ką sakai”. Jis išėjo į prieškiemį, ir pragydo gaidys.
69ገረዲቱም አይታው በዚያ ለቆሙት። ይህም ከእነርሱ ወገን ነው ስትል ሁለተኛ ትነግራቸው ጀመር።
69Pamačiusi jį, tarnaitė vėl pradėjo sakyti aplink stovėjusiems: “Šitas yra iš jų!”
70እርሱም ደግሞ ካደ። ጥቂት ቈይተውም በዚያ የቆሙት ዳግመኛ ጴጥሮስን። የገሊላ ሰው ነህና ከእነርሱ ወገን በእውነት ነህ አሉት።
70Jis vėl išsigynė. Kiek vėliau šalia stovintieji sakė Petrui: “Tu tikrai vienas iš jų, juk tu irgi galilėjietis, ir tarmė tavo tokia”.
71እርሱ ግን። ይህን የምትሉትን ሰው አላውቀውም ብሎ ይረገምና ይምል ጀመር። ወዲያውም ዶሮ ሁለተኛ ጮኸ።
71Tada jis pradėjo keiktis ir prisiekinėti: “Aš nepažįstu to žmogaus, apie kurį jūs kalbate!”
72ጴጥሮስንም ኢየሱስ። ዶሮ ሁለት ጊዜ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለው ቃል ትዝ አለው፤ ነገሩንም አስቦ አለቀሰ።
72Gaidys pragydo antrą kartą. Petras atsiminė, ką jam sakė Jėzus: “Gaidžiui nė dukart nepragydus, tu tris kartus manęs išsiginsi”. Tai prisiminęs, jis pravirko.