Lithuanian

Amharic: New Testament

Matthew

10

1Pasišaukęs dvylika savo mokinių, Jis suteikė jiems valdžią netyrosioms dvasioms, kad išvarinėtų jas ir gydytų visas ligas bei negalias.
1አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን ወደ እርሱ ጠርቶ፥ እንዲያወጡአቸው በርኩሳን መናፍስት ላይ ደዌንና ሕማምንም ሁሉ እንዲፈውሱ ሥልጣን ሰጣቸው።
2Dvylikos apaštalų vardai: pirmasis Simonas, vadinamas Petru, ir jo brolis Andriejus; Zebediejaus sūnus Jokūbas ir jo brolis Jonas;
2የአሥራ ሁለቱም ሐዋርያት ስም ይህ ነው፤ መጀመሪያው ጴጥሮስ የተባለው ስምዖን ወንድሙ እንድርያስም፥ የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብም ወንድሙ ዮሐንስም፥
3Pilypas ir Baltramiejus; Tomas ir muitininkas Matas; Alfiejaus sūnus Jokūbas ir Lebėjus, vadinamas Tadu;
3ፊልጶስም በርተሎሜዎስም፥ ቶማስም ቀራጩ ማቴዎስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም ታዴዎስም የተባለው ልብድዮስ፥
4Simonas Kananietis ir Judas Iskarijotas, kuris išdavė Jėzų.
4ቀነናዊውም ስምዖን ደግሞም አሳልፎ የሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ።
5Šiuos dvylika Jėzus išsiuntė, įsakydamas jiems: “Nepasukite keliu pas pagonis ir neužeikite į samariečių miestą,
5እነዚህን አሥራ ሁለቱን ኢየሱስ ላካቸው፥ አዘዛቸውም፥ እንዲህም አለ። በአሕዛብ መንገድ አትሂዱ፥ ወደ ሳምራውያንም ከተማ አትግቡ፤
6bet verčiau eikite pas pražuvusias Izraelio namų avis.
6ይልቅስ የእስራኤል ቤት ወደሚሆኑ ወደ ጠፉት በጎች ሂዱ እንጂ።
7Keliaudami skelbkite: ‘Prisiartino dangaus karalystė!’
7ሄዳችሁም። መንግሥተ ሰማያት ቀርባለች ብላችሁ ስበኩ።
8Gydykite ligonius, apvalykite raupsuotuosius, prikelkite mirusius, išvarinėkite demonus. Dovanai gavote, dovanai ir duokite!
8ድውዮችን ፈውሱ፤ ሙታንን አስነሡ፤ ለምጻሞችን አንጹ፤ አጋንንትን አውጡ፤ በከንቱ ተቀበላችሁ፥ በከንቱ ስጡ።
9Neimkite nei aukso, nei sidabro, nei variokų į savo juostas;
9ወርቅ ወይም ብር ወይም ናስ በመቀነታችሁ፥
10nei kelionmaišio, nei dviejų tunikų, nei sandalų, nei lazdos, nes darbininkas vertas savo valgio.
10ወይም ለመንገድ ከረጢት ወይም ሁለት እጀ ጠባብ ወይም ጫማ ወይም በትር አታግኙ፤ ለሠራተኛ ምግቡ ይገባዋልና።
11Atėję į kokį nors miestą ar kaimą, susiieškokite vertą žmogų ir apsistokite pas jį, kol išvyksite.
11በምትገቡባትም በማናቸይቱም ከተማ ወይም መንደር፥ በዚያ የሚገባው ማን እንደ ሆነ በጥንቃቄ መርምሩ፤ እስክትወጡም ድረስ በዚያ ተቀመጡ።
12Įeidami į namus, pasveikinkite juos.
12ወደ ቤትም ስትገቡ ሰላምታ ስጡ፤
13Ir jeigu namai bus verti, teateinie jiems jūsų ramybė. O jeigu nebus verti­jūsų ramybė tesugrįžta jums.
13ቤቱም የሚገባው ቢሆን ሰላማችሁ ይድረስለት፤ ባይገባው ግን ሰላማችሁ ይመለስላችሁ።
14Jei kas jūsų nepriimtų ir neklausytų jūsų žodžių, tai, išėję iš tokių namų ar tokio miesto, nusikratykite ir dulkes nuo kojų.
14ከማይቀበላችሁም ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ፥ ከዚያ ቤት ወይም ከዚያች ከተማ ስትወጡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ።
15Iš tiesų sakau jums: Sodomos ir Gomoros žemei bus lengviau teismo dieną negu tokiam miestui”.
15እውነት እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ አገር ይቀልላቸዋል።
16“Štai Aš siunčiu jus kaip avis tarp vilkų. Todėl būkite gudrūs kaip žalčiai ir neklastingi kaip balandžiai.
16እነሆ፥ እኔ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ።
17Saugokitės žmonių, nes jie įskųs jus teismams ir plaks savo sinagogose.
17ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ በምኩራቦቻቸውም ይገርፉአችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ፤
18Jūs būsite dėl manęs vedžiojami pas valdytojus ir karalius liudyti jiems ir pagonims.
18ለእነርሱና ለአሕዛብም ምስክር እንዲሆን፥ ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ።
19Kai jie jus įskųs, nesirūpinkite, kaip arba ką kalbėsite, nes tą valandą jums bus duota, ką jūs turite sakyti.
19አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤
20Nes ne jūs kalbėsite, o jūsų Tėvo Dvasia kalbės jumyse.
20በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና።
21Brolis išduos mirti brolį ir tėvas­sūnų, o vaikai sukils prieš gimdytojus ir žudys juos.
21ወንድምም ወንድሙን፥ አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ ይገድሉአቸውማል።
22Jūs būsite visų nekenčiami dėl mano vardo. Bet kas ištvers iki galo, bus išgelbėtas.
22በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል።
23Kai jus persekios viename mieste, bėkite į kitą. Iš tiesų sakau jums: dar nebūsite išvaikščioję Izraelio miestų, kai ateis Žmogaus Sūnus.
23በአንዲቱ ከተማም መከራ ቢያሳዩአችሁ ወደ ሌላይቱ ሽሹ፤ እውነት እላችኋለሁና፥ የሰው ልጅ እስኪመጣ ድረስ የእስራኤልን ከተማዎች አትዘልቁም።
24Mokinys nėra aukštesnis už savo mokytoją nei tarnas už šeimininką.
24ደቀ መዝሙር ከመምህሩ፥ ባሪያም ከጌታው አይበልጥም።
25Pakanka, jei mokinys prilygsta mokytojui ir tarnas šeimininkui. Jei namų šeimininką jie praminė Belzebulu, tai ką bekalbėti apie namiškius!”
25ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ፥ ባሪያም እንደ ጌታው መሆኑ ይበቃዋል። ባለቤቱን ብዔል ዜቡል ካሉት፥ ቤተሰዎቹንማ እንዴት አብዝተው አይሉአቸው!
26“Taigi nebijokite jų. Nes nieko nėra uždengta, kas nebus atidengta, ir nieko paslėpta, kas nepasidarys žinoma.
26እንግዲህ አትፍሩአቸው፤ የማይገለጥ የተከደነ፥ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለምና።
27Ką jums kalbu tamsoje, sakykite šviesoje, ir ką šnibždu į ausį, skelbkite nuo stogų.
27በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ፤ በጆሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ።
28Nebijokite tų, kurie žudo kūną, bet negali užmušti sielos. Verčiau bijokite to, kuris gali pražudyti ir sielą, ir kūną pragare.
28ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ።
29Argi ne du žvirbliai parduodami už skatiką? Ir nė vienas iš jų nekrinta žemėn be jūsų Tėvo valios.
29ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ከእነርሱም አንዲቱ ያለ አባታችሁ ፈቃድ በምድር ላይ አትወድቅም።
30O jūsų net visi galvos plaukai suskaičiuoti.
30የእናንተስ የራሳችሁ ጠጉር ሁሉ እንኳ ተቈጥሮአል።
31Tad nebijokite! Jūs vertesni už daugybę žvirblių.
31እንግዲህ አትፍሩ ከብዙ ድንቢጦች እናንተ ትበልጣላችሁ።
32Kas išpažins mane žmonių akivaizdoje, ir Aš jį išpažinsiu savo dangiškojo Tėvo akivaizdoje.
32ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤
33O kas išsižadės manęs žmonių akivaizdoje, ir Aš jo išsižadėsiu savo dangiškojo Tėvo akivaizdoje”.
33በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ።
34“Nemanykite, jog Aš atėjau atnešti žemėn ramybės. Atėjau atnešti ne ramybės, o kalavijo.
34በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም።
35Atėjau sukiršinti ‘sūnaus prieš tėvą, dukters prieš motiną ir marčios prieš anytą.
35ሰውን ከአባቱ፥ ሴት ልጅንም ከእናትዋ፥ ምራትንም ከአማትዋ እለያይ ዘንድ መጥቻለሁና፤
36Žmogaus namiškiai taps jam priešais’.
36ለሰውም ቤተ ሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል።
37Kas myli tėvą ar motiną labiau negu mane­nevertas manęs. Kas myli sūnų ar dukterį labiau negu mane­nevertas manęs.
37ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤
38Kas neima savo kryžiaus ir neseka paskui mane, tas nevertas manęs.
38መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም።
39Kas išsaugo savo gyvybę, praras ją, o kas praranda savo gyvybę dėl manęs­atras ją.
39ነፍሱን የሚያገኝ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም ስለ እኔ የሚያጠፋ ያገኛታል።
40Kas jus priima, tas mane priima. O kas priima mane, priima Tą, kuris mane siuntė.
40እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።
41Kas priima pranašą dėl to, kad jis pranašas, gaus pranašo atlygį. Kas priima teisųjį dėl to, kad jis teisusis, gaus teisiojo atlygį.
41ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።
42Ir kas paduos bent taurę šalto vandens vienam iš šitų mažųjų dėl to, kad jis yra mokinys,­iš tiesų sakau jums,­tas nepraras savo atlygio”.
42ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።