Lithuanian

Amharic: New Testament

Matthew

13

1Tą dieną, išėjęs iš namų, Jėzus atsisėdo ant ežero kranto.
1በዚያን ቀን ኢየሱስ ከቤት ወጥቶ በባሕር አጠገብ ተቀመጠ፤
2Prie Jo susirinko didžiulė minia; todėl Jis įlipo į valtį ir atsisėdo, o žmonės stovėjo pakrantėje.
2እርሱም በታንኳ ገብቶ እስኪቀመጥ ድረስ ብዙ ሰዎች ወደ እርሱ ተሰበሰቡ፥ ሕዝቡም ሁሉ በወደቡ ቆመው ነበር።
3Jis daug jiems kalbėjo palyginimais: “Štai sėjėjas išėjo sėti.
3በምሳሌም ብዙ ነገራቸው እንዲህም አላቸው። እነሆ፥ ዘሪ ሊዘራ ወጣ።
4Jam besėjant, vieni grūdai nukrito palei kelią, ir atskridę paukščiai juos sulesė.
4እርሱም ሲዘራ አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀ፥ ወፎችም መጥተው በሉት።
5Kiti nukrito uolėtoj vietoj, kur buvo nedaug žemės. Jie greit sudygo, nes neturėjo gilesnio žemės sluoksnio.
5ሌላውም ብዙ መሬት በሌለበት በጭንጫ ላይ ወደቀ፤ ጥልቅ መሬትም ስላልነበረው ወዲያው በቀለ፥
6Saulei patekėjus, daigai išdegė ir, neturėdami šaknų, sudžiūvo.
6ፀሐይ በወጣ ጊዜ ግን ጠወለገ፥ ሥርም ስላልነበረው ደረቀ።
7Kiti nukrito tarp erškėčių. Erškėčiai išaugo ir nusmelkė juos.
7ሌላውም በእሾህ መካከል ወደቀ፥ እሾህም ወጣና አነቀው።
8Dar kiti nukrito į gerą žemę ir davė derlių: vieni šimteriopą, kiti šešiasdešimteriopą, dar kiti trisdešimteriopą.
8ሌላውም በመልካም መሬት ወደቀ፤ አንዱም መቶ፥ አንዱም ስድሳ፥ አንዱም ሠላሳ ፍሬ ሰጠ።
9Kas turi ausis klausyti­teklauso!”
9የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።
10Priėję mokiniai paklausė Jo: “Kodėl jiems kalbi palyginimais?”
10ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው። ስለ ምን በምሳሌ ትነግራቸዋለህ? አሉት።
11Jėzus atsakė: “Jums duota pažinti dangaus karalystės paslaptis, o jiems neduota.
11እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው። ለእናንተ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፥ ለእነርሱ ግን አልተሰጣቸውም።
12Mat, kas turi, tam bus duota, ir jis turės su pertekliumi, o iš neturinčio bus atimta ir tai, ką jis turi.
12ላለው ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል።
13Aš jiems kalbu palyginimais todėl, kad jie žiūrėdami nemato, klausydami negirdi ir nesupranta.
13ስለዚህ እያዩ ስለማያዩ እየሰሙም ስለማይሰሙ ስለማያስተውሉም በምሳሌ እነግራቸዋለሁ።
14Jiems pildosi Izaijo pranašystės žodžiai: ‘Girdėti girdėsite, bet nesuprasite, žiūrėti žiūrėsite, bet nematysite.
14መስማት ትሰማላችሁና አታስተውሉም፥ ማየትም ታያላችሁና አትመለከቱም።
15Šitų žmonių širdys aptuko. Jie prastai girdėjo ausimis ir užmerkė akis, kad nepamatytų akimis, neišgirstų ausimis, nesuprastų širdimi ir neatsiverstų, ir Aš jų nepagydyčiau’.
15በዓይናቸው እንዳያዩ፥ በጆሮአቸውም እንዳይሰሙ፥ በልባቸውም እንዳያስተውሉ፥ ተመልሰውም እንዳልፈውሳቸው፥ የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአልና ጆሮአቸውም ደንቁሮአል ዓይናቸውንም ጨፍነዋል የሚል የኢሳይያስ ትንቢት በእነርሱ ይፈጸማል።
16Bet palaimintos jūsų akys, nes mato, ir jūsų ausys, nes girdi.
16የእናንተ ግን ዓይኖቻችሁ ስለሚያዩ ጆሮቻችሁም ስለሚሰሙ ብፁዓን ናቸው።
17Iš tiesų sakau jums: daugelis pranašų ir teisiųjų troško išvysti, ką jūs matote, bet neišvydo, ir girdėti, ką jūs girdite, bet neišgirdo”.
17እውነት እላችኋለሁ፥ ብዙዎች ነቢያትና ጻድቃን የምታዩትን ሊያዩ ተመኝተው አላዩም፥ የምትሰሙትንም ሊሰሙ ተመኝተው አልሰሙም።
18“Tad pasiklausykite palyginimo apie sėjėją.
18እንግዲህ እናንተ የዘሪውን ምሳሌ ስሙ።
19Pas kiekvieną, kuris girdi karalystės žodį ir nesupranta, ateina piktasis ir išplėšia, kas buvo pasėta jo širdyje. Tai yra pasėlis prie kelio.
19የመንግሥትን ቃል ሰምቶ በማያስተውል ሁሉ፥ ክፉው ይመጣል፥ በልቡ የተዘራውንም ይነጥቃል፤ በመንገድ ዳር የተዘራው ይህ ነው።
20Pasėlis uolėtoje vietoje­tai tas, kuris, girdėdamas žodį, tuojau su džiaugsmu jį priima.
20በጭንጫ ላይ የተዘራውም ይህ ቃሉን ሰምቶ ወዲያው በደስታ የሚቀበለው ነው፤
21Tačiau jis be šaknų­nepastovus žmogus. Kilus kokiam sunkumui ar persekiojimui dėl žodžio, jis tuoj pat pasipiktina.
21ነገር ግን ለጊዜው ነው እንጂ በእርሱ ሥር የለውም፥ በቃሉ ምክንያትም መከራ ወይም ስደት በሆነ ጊዜ ወዲያው ይሰናከላል።
22Pasėlis tarp erškėčių­tai tas, kuris klauso žodžio, bet šio pasaulio rūpesčiai ir turtų apgaulė nustelbia žodį, ir jis lieka nevaisingas.
22በእሾህ መካከል የተዘራውም ይህ ቃሉን የሚሰማ ነው፥ የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት መታለል ቃሉን ያንቃል፥ የማያፈራም ይሆናል።
23O pasėlis geroje žemėje­tas, kuris girdi ir supranta žodį; tas ir neša vaisių: kas duoda šimteriopą, kas šešiasdešimteriopą, o kas trisdešimteriopą”.
23በመልካም መሬት የተዘራውም ይህ ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውል ነው፤ እርሱም ፍሬ ያፈራል አንዱም መቶ አንዱም ስድሳ አንዱም ሠላሳ ያደርጋል።
24Jis pateikė jiems kitą palyginimą: “Su dangaus karalyste yra kaip su žmogumi, kuris pasėjo dirvoje gerą sėklą.
24ሌላ ምሳሌ አቀረበላቸው እንዲህም አለ። መንግሥተ ሰማያት በእርሻው መልካም ዘርን የዘራን ሰው ትመስላለች።
25Žmonėms bemiegant, atėjo jo priešas, pasėjo kviečiuose raugių ir nuėjo.
25ሰዎቹ ሲተኙ ግን ጠላቱ መጣና በስንዴው መካከል እንክርዳድን ዘርቶ ሄደ።
26Kai želmuo paūgėjo ir subrandino vaisių, pasirodė ir raugės.
26ስንዴውም በበቀለና በአፈራ ጊዜ እንክርዳዱ ደግሞ ያን ጊዜ ታየ።
27Šeimininko tarnai atėję klausė: ‘Šeimininke, argi ne gerą sėklą pasėjai savo lauke? Iš kurgi atsirado raugių?’
27የባለቤቱም ባሮች ቀርበው። ጌታ ሆይ፥ መልካምን ዘር በእርሻህ ዘርተህ አልነበርህምን? እንክርዳዱንስ ከወዴት አገኘ? አሉት።
28Jis atsakė: ‘Tai padarė priešas’. Tarnai pasiūlė: ‘Jei nori, eisime ir jas išravėsime’.
28እርሱም። ጠላት ይህን አደረገ አላቸው። ባሮቹም። እንግዲህ ሄደን ብንለቅመው ትወዳለህን? አሉት።
29Jis atsakė: ‘Ne, kad kartais, ravėdami rauges, neišrautumėte kartu su jomis ir kviečių.
29እርሱ ግን። እንክርዳዱን ስትለቅሙ ስንዴውን ከእርሱ ጋር እንዳትነቅሉት አይሆንም።
30Palikite abejus augti iki pjūties. Pjūties metu pasakysiu pjovėjams: ‘Pirmiau išrinkite rauges ir suriškite į pėdelius sudeginti, o kviečius sukraukite į mano kluoną’ ”.
30ተዉአቸው፤ እስከ መከር ጊዜ አብረው ይደጉ፤ በመከር ጊዜም አጫጆችን። እንክርዳዱን አስቀድማችሁ ልቀሙ በእሳትም ለማቃጠል በየነዶው እሰሩ፥ ስንዴውን ግን በጎተራዬ ክተቱ እላለሁ አለ።
31Jis pateikė jiems dar vieną palyginimą: “Dangaus karalystė yra kaip garstyčios grūdelis, kurį žmogus ėmė ir pasėjo savo dirvoje.
31ሌላ ምሳሌ አቀረበላቸው እንዲህም አለ። መንግሥተ ሰማያት ሰው ወስዶ በእርሻው የዘራትን የሰናፍጭ ቅንጣት ትመስላለች፤
32Nors jis mažiausias iš visų sėklų, bet užaugęs būna didesnis už visus augalus ir tampa medeliu; net padangių paukščiai atskridę susisuka lizdus jo šakose”.
32እርስዋም ከዘር ሁሉ ታንሳለች፥ በአደገች ጊዜ ግን፥ ከአታክልቶች ትበልጣለች የሰማይም ወፎች መጥተው በቅርንጫፎችዋ እስኪሰፍሩ ድረስ ዛፍ ትሆናለች።
33Jis pasakė ir dar kitą palyginimą: “Dangaus karalystė yra kaip raugas, kurį moteris įmaišė trijuose saikuose miltų, ir nuo jo viskas įrūgo”.
33ሌላ ምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ። መንግሥተ ሰማያት ሁሉ እስኪቦካ ድረስ ሴት ወስዳ በሦስት መስፈሪያ ዱቄት የሸሸገችውን እርሾ ትመስላለች።
34Visa tai Jėzus kalbėjo minioms palyginimais, ir be palyginimų Jis jiems nekalbėjo,
34ኢየሱስም ለሕዝቡ ይህን ሁሉ በምሳሌ ተናገረ፤ በነቢዩም። በምሳሌ አፌን እከፍታለሁ፥ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የተሰወረውንም እናገራለሁ የተባለው ይፈጸም ዘንድ ያለ ምሳሌ አልተናገራቸውም።
35kad išsipildytų, kas buvo per pranašą pasakyta: “Aš atversiu savo burną palyginimais, skelbsiu nuo pasaulio sukūrimo paslėptus dalykus”.
36በዚያን ጊዜ ሕዝቡን ትቶ ወደ ቤት ገባ። ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ ቀርበው። የእርሻውን እንክርዳድ ምሳሌ ተርጕምልን አሉት።
36Paleidęs minias, Jėzus parėjo namo. Prie Jo priėjo mokiniai ir prašė: “Išaiškink mums palyginimą apie rauges dirvoje”.
37እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው። መልካምን ዘር የዘራው የሰው ልጅ ነው፤ እርሻውም ዓለም ነው፤
37Jis jiems atsakė: “Sėjantysis gerą sėklą yra Žmogaus Sūnus.
38መልካሙም ዘር የመንግሥት ልጆች ናቸው፤
38Dirva­tai pasaulis. Gera sėkla­karalystės vaikai, o raugės­ piktojo vaikai.
39እንክርዳዱም የክፉው ልጆች ናቸው፥ የዘራውም ጠላት ዲያብሎስ ነው፤ መከሩም የዓለም መጨረሻ ነው፥ አጫጆችም መላእክት ናቸው።
39Jas pasėjęs priešas­velnias. Pjūtis­pasaulio pabaiga, o pjovėjai­ angelai.
40እንግዲህ እንክርዳድ ተለቅሞ በእሳት እንደሚቃጠል፥ በዓለም መጨረሻ እንዲሁ ይሆናል።
40Taigi, kaip surenkamos ir sudeginamos ugnyje raugės, taip bus ir pasaulio pabaigoje.
41የሰው ልጅ መላእክቱን ይልካል፥ ከመንግሥቱም እንቅፋትን ሁሉ ዓመፃንም የሚያደርጉትን ይለቅማሉ፥
41Žmogaus Sūnus išsiųs savo angelus, tie išrankios iš Jo karalystės visus papiktinimus bei piktadarius
42ወደ እቶነ እሳትም ይጥሉአቸዋል፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።
42ir įmes juos į ugnies krosnį. Ten bus verksmas ir dantų griežimas.
43በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።
43Tada teisieji spindės kaip saulė savo Tėvo karalystėje. Kas turi ausis klausyti­teklauso!”
44ደግሞ መንግሥተ ሰማያት በእርሻ ውስጥ የተሰወረውን መዝገብ ትመስላለች፤ ሰውም አግኝቶ ሰወረው፥ ከደስታውም የተነሣ ሄዶ ያለውን ሁሉ ሸጠና ያን እርሻ ገዛ።
44“Dangaus karalystė yra kaip dirvoje paslėptas lobis. Atradęs jį, žmogus tai nuslepia; iš to džiaugsmo eina, parduoda visa, ką turi, ir perka tą dirvą.
45ደግሞ መንግሥተ ሰማያት መልካምን ዕንቁ የሚሻ ነጋዴን ትመስላለች፤
45Vėl su dangaus karalyste yra kaip su pirkliu, ieškančiu gerų perlų.
46ዋጋዋም እጅግ የበዛ አንዲት ዕንቁ በአገኘ ጊዜ ሄዶ ያለውን ሁሉ ሸጠና ገዛት።
46Atradęs vieną brangų perlą, jis eina, parduoda visa, ką turi, ir nusiperka jį”.
47ደግሞ መንግሥተ ሰማያት ወደ ባሕር የተጣለች ከሁሉም ዓይነት የሰበሰበች መረብን ትመስላለች፤
47“Ir vėl su dangaus karalyste yra kaip su jūron metamu tinklu, užgriebiančiu įvairiausių žuvų.
48በሞላችም ጊዜ ወደ ወደቡ አወጡአት፥ ተቀምጠውም መልካሙን ለቅመው በዕቃዎች ውስጥ አከማቹ ክፉውን ግን ወደ ውጭ ጣሉት።
48Kai jis pilnas, jį išvelka į krantą, susėda ir surenka gerąsias į indus, o blogąsias išmeta.
49በዓለም መጨረሻ እንዲሁ ይሆናል፤ መላእክት መጥተው ኃጢአተኞችን ከጻድቃን መካከል ይለዩአቸዋል፥ ወደ እቶነ እሳትም ይጥሉአቸዋል፤
49Taip bus ir pasaulio pabaigoje: išeis angelai, išrankios bloguosius iš gerųjų
50በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።
50ir įmes juos į ugnies krosnį. Ten bus verksmas ir dantų griežimas”.
51ኢየሱስም። ይህን ሁሉ አስተዋላችሁን? አላቸው አዎን አሉት።
51Jėzus paklausė jų: “Ar supratote visa tai?” Jie atsakė: “Taip, Viešpatie”.
52እርሱም። ስለዚህ የመንግሥተ ሰማያት ደቀ መዝሙር የሆነ ጻፊ ሁሉ ከመዝገቡ አዲሱንና አሮጌውን የሚያወጣ ባለቤትን ይመስላል አላቸው።
52Tada Jis jiems tarė: “Todėl kiekvienas Rašto žinovas, tapęs dangaus karalystės mokiniu, panašus į šeimininką, kuris iškelia iš savo lobyno naujų ir senų daiktų”.
53ኢየሱስም እነዚህም ምሳሌዎች ከጨረሰ በኋላ ከዚያ ሄደ።
53Baigęs sakyti tuos palyginimus, Jėzus iškeliavo iš ten.
54ወደ ገዛ አገሩም መጥቶ እስኪገረሙ ድረስ በምኩራባቸው ያስተምራቸው ነበር፤ እንዲህም አሉ። ይህን ጥበብና ተአምራት ይህ ከወዴት አገኘው?
54Jis parėjo į savo tėviškę ir mokė žmones jų sinagogoje taip, kad jie stebėjosi ir klausinėjo: “Iš kur šitam tokia išmintis ir stebuklingi darbai?
55ይህ የጸራቢ ልጅ አይደለምን? እናቱስ ማርያም ትባል የለምን? ወንድሞቹስ ያዕቆብና ዮሳ ስምዖንም ይሁዳም አይደሉምን?
55Argi Jis ne dailidės sūnus?! Argi Jo motina nesivadina Marija, o Jokūbas, Jozė, Simonas ir Judas argi ne Jo broliai?
56እኅቶቹስ ሁሉ በእኛ ዘንድ ያሉ አይደሉምን? እንኪያስ ይህን ሁሉ ከወዴት አገኘው? ተሰናከሉበትም።
56Ir Jo seserys­argi jos ne visos yra pas mus? Iš kur Jam visa tai?”
57ኢየሱስ ግን። ነቢይ ከገዛ አገሩና ከገዛ ቤቱ በቀር ሳይከበር አይቀርም አላቸው።
57Ir jie ėmė piktintis Juo. O Jėzus jiems atsakė: “Pranašas nebūna be pagarbos, nebent savo tėviškėje ir savo namuose”.
58በአለማመናቸውም ምክንያት በዚያ ብዙ ተአምራት አላደረገም።
58Ir Jis ten nedarė daug stebuklų dėl jų netikėjimo.