Lithuanian

Amharic: New Testament

Matthew

14

1Anuo metu garsas apie Jėzų pasiekė tetrarchą Erodą,
1በዚያ ዘመን የአራተኛው ክፍል ገዥ ሄሮድስ የኢየሱስን ዝና ሰማ፥
2ir jis savo tarnams pasakė: “Tai Jonas Krikštytojas! Jis prisikėlė iš numirusių, ir todėl jame veikia stebuklingos jėgos”.
2ለሎሌዎቹም። ይህ መጥምቁ ዮሐንስ ነው፤ እርሱ ከሙታን ተነሥቶአል፥ ስለዚህም ኃይል በእርሱ ይደረጋል አለ።
3Mat Erodas buvo suėmęs Joną, sukaustęs jį ir įmetęs į kalėjimą dėl savo brolio Pilypo žmonos Erodiados.
3ሄሮድስ በወንድሙ በፊልጶስ ሚስት በሄሮድያዳ ምክንያት ዮሐንስን አስይዞ አሳስሮት በወህኒ አኑሮት ነበርና፤
4Nes Jonas jam sakė: “Tau nevalia jos turėti”.
4ዮሐንስ። እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም ይለው ነበርና።
5Erodas norėjo nužudyti Joną, bet bijojo žmonių, nes jie laikė jį pranašu.
5ሊገድለውም ወዶ ሳለ፥ ሕዝቡ እንደ ነቢይ ስለ አዩት ፈራቸው።
6Erodo gimimo dieną Erodiados duktė šoko svečiams ir patiko Erodui.
6ነገር ግን ሄሮድስ የተወለደበት ቀን በሆነ ጊዜ፥ የሄሮድያዳ ልጅ በመካከላቸው ዘፈነች ሄሮድስንም ደስ አሰኘችው፤
7Todėl jis su priesaika pažadėjo jai duoti, ko tik ji paprašys.
7ስለዚህም የምትለምነውን ሁሉ እንዲሰጣት በመሐላ ተስፋ አደረገላት።
8O ši, savo motinos primokyta, tarė: “Duok man čia dubenyje Jono Krikštytojo galvą”.
8እርስዋም በእናትዋ ተመክራ። የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በዚህ በወጭት ስጠኝ አለችው።
9Karalius nuliūdo, bet dėl priesaikos ir svečių įsakė duoti.
9ንጉሡም አዘነ፥ ነገር ግን ስለ መሐላው ከእርሱም ጋር ተቀምጠው ስላሉት ሰዎች እንዲሰጡአት አዘዘ፤
10Jis pasiuntė nukirsti kalėjime Jonui galvą.
10ልኮም የዮሐንስን ራስ በወህኒ አስቆረጠው።
11Jo galva buvo atnešta dubenyje ir įteikta mergaitei, kuri ją nunešė motinai.
11ራሱንም በወጭት አምጥተው ለብላቴናይቱ ሰጡአት፥ ወደ እናትዋም ወሰደችው።
12Jono mokiniai atėję pasiėmė kūną, palaidojo ir nuėję pranešė Jėzui.
12ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው በድኑን ወሰዱና ቀበሩት፥ መጥተውም ለኢየሱስ አወሩለት።
13Tai išgirdęs, Jėzus valtimi nuplaukė į dykvietę, į vienumą. Minios sužinojo ir iš miestų pėsčiomis nusekė paskui.
13ኢየሱስም በሰማ ጊዜ ከዚያ ብቻውን ወደ ምድረ በዳ በታንኳ ፈቀቅ አለ፤ ሕዝቡም ሰምተው ከከተማዎቹ በእግር ተከተሉት።
14Išlipęs Jėzus pamatė daugybę žmonių. Jėzui pagailo jų, ir Jis išgydė jų ligonius.
14ወጥቶም ብዙ ሕዝብ አየና አዘነላቸው ድውዮቻቸውንም ፈወሰ።
15Atėjus vakarui, priėjo mokiniai ir tarė: “Čia dykvietė, ir jau vėlus metas. Paleisk žmones, kad, nuėję į kaimus, nusipirktų maisto”.
15በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበው። ቦታው ምድረ በዳ ነው አሁንም ሰዓቱ አልፎአል፤ ወደ መንደሮች ሄደው ለራሳቸው ምግብ እንዲገዙ ሕዝቡን አሰናብት አሉት።
16Bet Jėzus jiems atsakė: “Nėra reikalo jiems iš čia eiti. Jūs duokite jiems valgyti”.
16ኢየሱስም። እናንተ የሚበሉትን ስጡአቸው እንጂ ሊሄዱ አያስፈልግም አላቸው።
17Jie atsiliepė: “Mes čia turime tik penkis kepalus duonos ir dvi žuvis”.
17እነርሱም። ከአምስት እንጀራና ከሁለት ዓሣ በቀር በዚህ የለንም አሉት።
18Jis tarė: “Atneškite juos man”.
18እርሱም። እነዚያን ወደዚህ አምጡልኝ አላቸው።
19Ir, liepęs miniai susėsti ant žolės, Jis paėmė penkis duonos kepalus ir dvi žuvis, pažvelgė į dangų, palaimino, laužė ir davė kepalus mokiniams, o tie dalijo žmonėms.
19ሕዝቡም በሣር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፥ አምስቱንም እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ወደ ሰማይ አሻቅቦ አየና ባረከ፥ እንጀራውንም ቆርሶ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ።
20Visi valgė ir pasisotino. Ir surinko dvylika pilnų pintinių likusių trupinių.
20ሁሉም በልተው ጠገቡ፥ የተረፈውንም ቁርስራሽ አሥራ ሁለት መሶብ ሙሉ አነሡ።
21O valgytojų buvo apie penkis tūkstančius vyrų, neskaičiuojant moterų ir vaikų.
21ከሴቶችና ከልጆችም በቀር የበሉት አምስት ሺህ ወንዶች ያህሉ ነበር።
22Tuojau pat Jėzus privertė savo mokinius sėsti į valtį ir pirma Jo plaukti į kitą ežero pusę, kol Jis paleisiąs minią.
22ወዲያውም ሕዝቡን ሲያሰናብት ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ በታንኳይቱ ገብተው ወደ ማዶ እንዲቀድሙት ግድ አላቸው።
23Paleidęs minią, Jis užkopė nuošaliai į kalną melstis. Atėjus vakarui, Jis buvo ten vienas.
23ሕዝቡንም አሰናብቶ ይጸልይ ዘንድ ብቻውን ወደ ተራራ ወጣ። በመሸም ጊዜ ብቻውን በዚያ ነበረ።
24Tuo tarpu valtis jau buvo ežero viduryje, blaškoma bangų, nes pūtė priešingas vėjas.
24ታንኳይቱም አሁን በባሕር መካከል ሳለች፥ ነፋስ ከወደ ፊት ነበርና በማዕበል ትጨነቅ ነበር።
25Ketvirtos nakties sargybos metu Jėzus atėjo pas juos, žengdamas ežero paviršiumi.
25ከሌሊቱም በአራተኛው ክፍል ኢየሱስ በባሕር ላይ እየሄደ ወደ እነርሱ መጣ።
26Pamatę Jį einantį ežero paviršiumi, mokiniai nusigando ir iš baimės ėmė šaukti: “Tai šmėkla!”
26ደቀ መዛሙርቱም በባሕር ላይ ሲሄድ ባዩት ጊዜ። ምትሐት ነው ብለው ታወኩ በፍርሃትም ጮኹ።
27Jėzus tuojau juos prakalbino: “Drąsos! Tai Aš. Nebijokite!”
27ወዲያውም ኢየሱስ ተናገራቸውና። አይዞአችሁ፥ እኔ ነኝ፤ አትፍሩ አላቸው።
28Petras atsiliepė: “Viešpatie, jei čia Tu, liepk man ateiti pas Tave vandeniu”.
28ጴጥሮስም መልሶ። ጌታ ሆይ፥ አንተስ ከሆንህ በውኃው ላይ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝ አለው።
29Jis atsakė: “Ateik!” Petras, išlipęs iš valties, ėjo vandeniu, norėdamas ateiti pas Jėzų.
29እርሱም። ና አለው። ጴጥሮስም ከታንኳይቱ ወርዶ ወደ ኢየሱስ ሊደርስ በውኃው ላይ ሄደ።
30Bet, pamatęs vėjo smarkumą, jis išsigando ir, pradėjęs skęsti, sušuko: “Viešpatie, gelbėk mane!”
30ነገር ግን የነፋሱን ኃይል አይቶ ፈራ፥ ሊሰጥምም በጀመረ ጊዜ። ጌታ ሆይ፥ አድነኝ ብሎ ጮኸ።
31Tuojau ištiesęs ranką, Jėzus sugriebė jį ir tarė: “Mažatiki, ko suabejojai?”
31ወዲያውም ኢየሱስ እጁን ዘርግቶ ያዘውና። አንተ እምነት የጎደለህ፥ ስለምን ተጠራጠርህ? አለው።
32Jiems įlipus į valtį, vėjas nurimo.
32ወደ ታንኳይቱም በወጡ ጊዜ ነፋሱ ተወ።
33Tie, kurie buvo valtyje, prisiartinę pagarbino Jį, sakydami: “Tikrai Tu esi Dievo Sūnus!”
33በታንኳይቱም የነበሩት። በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብለው ሰገዱለት።
34Perplaukę jie išlipo į krantą Genezarete.
34ተሻግረውም ወደ ጌንሴሬጥ ምድር መጡ።
35Pažinę Jį, tos vietos gyventojai pasiuntė į visas to krašto apylinkes ir sugabeno pas Jį visus sergančius.
35የዚያ ቦታ ሰዎችም ባወቁት ጊዜ በዙርያው ወዳለ አገር ሁሉ ላኩ፥ ሕመምተኞችንም ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ፤
36Jie maldavo Jį leisti palytėti nors Jo apsiausto apvadą. Ir kurie tik palietė­tapo visiškai sveiki.
36የልብሱንም ጫፍ ብቻ ሊዳስሱ ይለምኑት ነበር፤ የዳሰሱትም ሁሉ ዳኑ።