1Tuomet prie Jėzaus priėjo Rašto žinovų ir fariziejų iš Jeruzalės ir klausė:
1በዚያን ጊዜ ጻፎችና ፈሪሳውያን ከኢየሩሳሌም ወደ ኢየሱስ ቀረቡና።
2“Kodėl Tavo mokiniai laužo prosenių tradiciją? Jie, prieš valgydami duoną, nesiplauna rankų”.
2ደቀ መዛሙርትህ ስለ ምን የሽማግሎችን ወግ ይተላለፋሉ? እንጀራ ሲበሉ እጃቸውን አይታጠቡምና አሉት።
3Jis, atsakydamas jiems, tarė: “O kodėl ir jūs laužote Dievo įsakymą savo tradicija?!
3እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው። እናንተስ ስለ ወጋችሁ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ስለ ምን ትተላለፋላችሁ?
4Juk Dievas įsakė: ‘Gerbk savo tėvą ir motiną!’, ir: ‘Kas keiktų tėvą ar motiną, mirtimi temiršta!’
4እግዚአብሔር። አባትህንና እናትህን አክብር፤ ደግሞ። አባቱን ወይም እናቱን የሰደበ ፈጽሞ ይሙት ብሎአልና፤
5O jūs sakote: ‘Kiekvienas, kas pasakys tėvui ar motinai:Viskas, kas tau būtų naudinga iš manęs, tebūnie dovana Dievui
5እናንተ ግን። አባቱን ወይም እናቱን። ከእኔ የምትጠቀምበት መባ ነው የሚል ሁሉ፥
6tas gali negerbti tėvo ir motinos’. Taip jūs savo tradicija Dievo įsakymą padarote negaliojantį.
6አባቱን ወይም እናቱን አያከብርም ትላላችሁ፤ ስለ ወጋችሁም የእግዚአብሔርን ቃል ሻራችሁ።
7Veidmainiai! Gerai apie jus pranašavo Izaijas:
7እናንተ ግብዞች፥ ኢሳይያስ ስለ እናንተ።
8‘Ši tauta artinasi prie manęs savo lūpomis ir gerbia mane savo liežuviu, bet jos širdis toli nuo manęs.
8ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል፥ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤
9Veltui jie mane garbina, žmogiškus priesakus paversdami mokymu’ ”.
9የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል ብሎ በእውነት ትንቢት ተናገረ።
10Sušaukęs minią, Jis kalbėjo: “Klausykite ir supraskite!
10ሕዝቡንም ጠርቶ። ስሙ አስተውሉም፤
11Ne kas patenka į burną, suteršia žmogų, bet kas išeina iš burnos, tai suteršia žmogų”.
11ሰውን የሚያረክሰው ወደ አፍ የሚገባ አይደለም፥ ከአፍ የሚወጣው ግን ሰውን የሚያረክሰው ይህ ነው አላቸው።
12Tada priėję Jo mokiniai pranešė: “Ar žinai, kad fariziejai pasipiktino, išgirdę tuos žodžius?”
12በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ቀርበው። ፈሪሳውያን ይህን ቃል ሰምተው እንደ ተሰናከሉ አወቅህን? አሉት።
13Jis atsakė: “Kiekvienas augalas, kurio nesodino mano dangiškasis Tėvas, bus išrautas.
13እርሱ ግን መልሶ። የሰማዩ አባቴ ያልተከለው ተክል ሁሉ ይነቀላል።
14Palikite juos! Jie akli aklųjų vadovai. O jeigu aklas aklą ves, abu į duobę įkris”.
14ተዉአቸው፤ ዕውሮችን የሚመሩ ዕውሮች ናቸው፤ ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ አለ።
15Tuomet Petras paprašė Jo: “Išaiškink mums tą palyginimą”.
15ጴጥሮስም መልሶ። ምሳሌውን ተርጕምልን አለው።
16Jėzus atsakė: “Ar ir jūs dar nesuprantate?!
16ኢየሱስም እንዲህ አለ። እናንተ ደግሞ እስካሁን የማታስተውሉ ናችሁን?
17Argi nesuprantate, kad visa, kas patenka į burną, eina į pilvą ir išmetama laukan?
17ወደ አፍ የሚገባ ሁሉ ወደ ሆድ አልፎ ወደ እዳሪ እንዲጣል አትመለከቱምን?
18O kas išeina iš burnos, eina iš širdies, ir tai suteršia žmogų.
18ከአፍ የሚወጣ ግን ከልብ ይወጣል፥ ሰውንም የሚያረክሰው ያ ነው።
19Iš širdies išeina pikti sumanymai, žmogžudystės, svetimavimai, paleistuvystės, vagystės, melagingi liudijimai, piktžodžiavimai.
19ከልብ ክፉ አሳብ፥ መግደል፥ ምንዝርነት፥ ዝሙት፥ መስረቅ፥ በውሸት መመስከር፥ ስድብ ይወጣልና።
20Šitie dalykai suteršia žmogų, o valgymas neplautomis rankomis žmogaus nesuteršia”.
20ሰውን የሚያረክሰው ይህ ነው እንጂ፥ ባልታጠበ እጅ መብላትስ ሰውን አያረክሰውም።
21Iš ten išėjęs, Jėzus pasitraukė į Tyro ir Sidono sritį.
21ኢየሱስም ከዚያ ወጥቶ ወደ ጢሮስና ወደ ሲዶና አገር ሄደ።
22Ir štai iš ano krašto atėjo moteris kanaanietė ir šaukė Jam: “Pasigailėk manęs, Viešpatie, Dovydo Sūnau! Mano dukterį baisiai kankina demonas!”
22እነሆም፥ ከነናዊት ሴት ከዚያ አገር ወጥታ። ጌታ ሆይ፥ የዳዊት ልጅ፥ ማረኝ፤ ልጄን ጋኔን ክፉኛ ይዞአታል ብላ ጮኸች።
23Bet Jėzus neatsakė nė žodžio. Tada priėjo mokiniai ir ėmė Jį maldauti: “Paleisk ją, nes ji šaukia mums iš paskos!”
23እርሱ ግን አንዳች አልመለሰላትም። ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው። በኋላችን ትጮኻለችና አሰናብታት እያሉ ለመኑት።
24Bet Jis atsakė: “Aš esu siųstas tik pas pražuvusias Izraelio namų avis”.
24እርሱም መልሶ። ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም አለ።
25Tada ji priėjusi Jį pagarbino ir tarė: “Viešpatie, padėk man!”
25እርስዋ ግን መጥታ። ጌታ ሆይ፥ እርዳኝ እያለች ሰገደችለት።
26Jis atsakė: “Nedera imti vaikų duoną ir mesti šunyčiams”.
26እርሱ ግን መልሶ። የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም አለ።
27O ji atsiliepė: “Taip, Viešpatie, bet ir šunyčiai ėda trupinius, nukritusius nuo jų šeimininko stalo”.
27እርስዋም። አዎን ጌታ ሆይ፤ ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ አለች።
28Tada Jėzus jai tarė: “O moterie, didis tavo tikėjimas! Tebūnie tau, kaip tu nori”. Ir tą pačią valandą jos duktė pasveiko.
28በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ። አንቺ ሴት፥ እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ዳነች።
29Iš ten išėjęs, Jėzus atvyko prie Galilėjos ežero. Jis užkopė ant kalno ir atsisėdo.
29ኢየሱስም ከዚያ አልፎ ወደ ገሊላ ባሕር አጠገብ መጣ፥ ወደ ተራራም ወጥቶ በዚያ ተቀመጠ።
30Prie Jo susirinko didžiulės minios, kurios atsigabeno su savimi luošų, aklų, nebylių, raišų ir daugelį kitokių. Žmonės suguldė juos prie Jėzaus kojų, o Jis pagydė juos.
30ብዙ ሕዝብም አንካሶችን፥ ዕውሮችንም፥ ዲዳዎችንም፥ ጉንድሾችንም፥ ሌሎችንም ብዙ ይዘው ወደ እርሱ ቀረቡ፥ በኢየሱስም እግር አጠገብ ጣሉአቸው፤ ፈወሳቸውም፤
31Minia stebėjosi, matydama nebylius kalbančius, luošius išgijusius, raišius vaikščiojančius ir akluosius reginčius. Ir jie šlovino Izraelio Dievą.
31ስለዚህም ሕዝቡ ዲዳዎች ሲናገሩ፥ ጉንድሾችም ሲድኑ፥ አንካሶችም ሲሄዱ፥ ዕውሮችም ሲያዩ አይተው ተደነቁ፤ የእስራኤልንም አምላክ አከበሩ።
32Pasišaukęs savo mokinius, Jėzus tarė: “Gaila man minios, nes jau tris dienas jie pasilieka su manimi ir neturi ko valgyti. Aš nepaleisiu jų alkanų, kad nenusilptų kelyje”.
32ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን ጠርቶ። ሕዝቡ ከእኔ ጋር እስካሁን ሦስት ቀን ውለዋልና የሚበሉት ስለ ሌላቸው አዝንላቸዋለሁ፤ በመንገድም እንዳይዝሉ ጦማቸውን ላሰናብታቸው አልወድም አላቸው።
33Mokiniai Jam atsakė: “Iš kur mums imti dykumoje tiek duonos, kad galėtume pasotinti tokią didelę minią?”
33ደቀ መዛሙርቱም። ይህን ያህል ሕዝብ የሚያጠግብ ይህን ያህል እንጀራ በምድረ በዳ ከወዴት እናገኛለን? አሉት።
34Jėzus paklausė jų: “Kiek turite duonos?” Jie atsakė: “Septynis kepalus ir kelias žuveles”.
34ኢየሱስም። ስንት እንጀራ አላችሁ? አላቸው። እነርሱም። ሰባት፥ ጥቂትም ትንሽ ዓሣ አሉት።
35Jėzus liepė žmonėms susėsti ant žemės.
35ሕዝቡም በምድር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፤
36Tada paėmė septynis duonos kepalus ir žuvis, padėkojo, sulaužė ir davė savo mokiniams, o mokiniai miniai.
36ሰባቱንም እንጀራ ዓሣውንም ይዞ አመሰገነ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ።
37Visi valgė ir pasisotino. Ir surinko septynias pilnas pintines likusių trupinių.
37ሁሉም በሉና ጠገቡ፥ የተረፈውንም ቁርስራሽ ሰባት ቅርጫት ሙሉ አነሡ።
38O valgytojų buvo keturi tūkstančiai vyrų, neskaičiuojant moterų ir vaikų.
38የበሉትም ከሴቶችና ከልጆች በቀር አራት ሺህ ወንዶች ነበሩ።
39Paleidęs minią, Jis sėdo į valtį ir nuplaukė į Magadano sritį.
39ሕዝቡንም ካሰናበተ በኋላ ወደ ታንኳይቱ ገብቶ ወደ መጌዶል አገር መጣ።