Lithuanian

Amharic: New Testament

Matthew

16

1Atėjo fariziejų ir sadukiejų ir mėgindami prašė Jį parodyti jiems ženklą iš dangaus.
1ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያንም ቀርበው ሲፈትኑት ከሰማይ ምልክት እንዲያሳያቸው ለመኑት።
2Jis jiems atsakė: “Atėjus vakarui, jūs sakote: ‘Bus giedra, nes dangus raudonas’,
2እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው። በመሸ ጊዜ። ሰማዩ ቀልቶአልና ብራ ይሆናል ትላላችሁ፤
3ir rytmetį: ‘Šiandien bus lietaus, nes rausta apsiniaukęs dangus’. Veidmainiai! Jūs mokate atpažinti dangaus veidą, o laiko ženklų­ ne.
3ማለዳም። ሰማዩ ደምኖ ቀልቶአልና ዛሬ ይዘንባል ትላላችሁ። የሰማዩን ፊትማ መለየት ታውቃላችሁ፥ የዘመኑንስ ምልክት መለየት አትችሉምን?
4Pikta ir svetimaujanti karta ieško ženklo, tačiau jai nebus duota kito ženklo, kaip tik pranašo Jonos ženklas”. Ir, palikęs juos, nuėjo šalin.
4ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፥ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም። ትቶአቸውም ሄደ።
5Keldamiesi į kitą ežero pusę, mokiniai buvo užmiršę pasiimti duonos.
5ደቀ መዛሙርቱም ወደ ማዶ በመጡ ጊዜ እንጀራ መያዝን ረሱ።
6Jėzus jiems tarė: “Būkite atidūs ir saugokitės fariziejų bei sadukiejų raugo”.
6ኢየሱስም። ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን እርሾ ተጠንቀቁና ተጠበቁ አላቸው።
7O jie tarpusavy svarstė: “Tai todėl, kad nepasiėmėme duonos”.
7እነርሱም። እንጀራ ባንይዝ ነው ብለው እርስ በርሳቸው ተነጋገሩ።
8Tai supratęs, Jėzus tarė: “Mažatikiai! Kodėl svarstote, kad nepasiėmėte duonos?
8ኢየሱስም አውቆ እንዲህ አላቸው። እናንተ እምነት የጐደላችሁ፥ እንጀራ ስለ ሌላችሁ ስለ ምን እርስ በርሳችሁ ትነጋገራላችሁ? ገና አታስተውሉምን?
9Argi dar nesuprantate? Ar neprisimenate penkių kepalų penkiems tūkstančiams ir kiek pintinių surinkote trupinių?
9ለአምስቱ ሺህ አምስቱ እንጀራ፥ ስንት መሶብም እንዳነሣችሁ ትዝ አይላችሁምን?
10Arba septynių kepalų keturiems tūkstančiams ir kiek pintinių surinkote trupinių?!
10ወይስ ለአራቱ ሺህ ሰባቱ እንጀራ፥ ስንት ቅርጫትም እንዳነሣችሁ ትዝ አይላችሁምን?
11Tad kaip nesuprantate, jog kalbėjau jums ne apie duoną. Fariziejų ir sadukiejų raugo saugokitės!”
11ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን እርሾ እንድትጠበቁ ብዬ ስለ እንጀራ እንዳልተናገርኋችሁ እንዴት አታስተውሉምን?
12Tada jie suprato, kad Jis liepė saugotis ne duonos raugo, bet fariziejų ir sadukiejų mokslo.
12እነርሱም ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን ትምህርት እንጂ ከእንጀራ እርሾ እንዲጠበቁ እንዳላላቸው ያን ጊዜ አስተዋሉ።
13Atėjęs į Pilypo Cezarėjos apylinkes, Jėzus paklausė savo mokinius: “Kuo žmonės mane, Žmogaus Sūnų, laiko?”
13ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን። ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ።
14Jie atsakė: “Vieni Jonu Krikštytoju, kiti Eliju, kiti Jeremiju ar dar kuriuo iš pranašų”.
14እነርሱም። አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት።
15Jis vėl paklausė: “O kuo jūs mane laikote?”
15እርሱም። እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።
16Tada Simonas Petras atsakė: “Tu esi Kristus, gyvojo Dievo Sūnus”.
16ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ። አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ።
17Jėzus jam atsakė: “Palaimintas tu, Simonai, Jonos sūnau, nes ne kūnas ir kraujas tau tai apreiškė, bet mano Tėvas, kuris yra danguje.
17ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ።
18Ir Aš tau sakau: tu esi Petras, ir ant šios uolos Aš pastatysiu savo bažnyčią, ir pragaro vartai jos nenugalės.
18እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም።
19Tau duosiu dangaus karalystės raktus; ką tu suriši žemėje, bus surišta ir danguje, ir ką tu atriši žemėje, bus atrišta ir danguje”.
19የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል።
20Tada Jis griežtai įsakė savo mokiniams niekam neskelbti, kad Jis yra Jėzus­Kristus.
20ያን ጊዜም እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ ለማንም እንዳይነግሩ ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው።
21Nuo tada Jėzus pradėjo aiškinti savo mokiniams, kad Jis turįs eiti į Jeruzalę ir daug iškentėti nuo vyresniųjų, aukštųjų kunigų ir Rašto žinovų, būti nužudytas ir trečią dieną prisikelti.
21ከዚያን ቀን ጀምሮ ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ይሄድ ዘንድ ከሽማግሎችና ከካህናት አለቆች ከጻፎችም ብዙ መከራ ይቀበልና ይገደል ዘንድ በሦስተኛውም ቀን ይነሣ ዘንድ እንዲገባው ለደቀ መዛሙርቱ ይገልጥላቸው ጀመር።
22Tada Petras, pasivadinęs Jį į šalį, ėmė drausti: “Jokiu būdu, Viešpatie, Tau neturi taip atsitikti!”
22ጴጥሮስም ወደ እርሱ ወስዶ። አይሁንብህ ጌታ ሆይ፤ ይህ ከቶ አይደርስብህም ብሎ ሊገሥጸው ጀመረ።
23Bet Jis atsisukęs pasakė Petrui: “Eik šalin, šėtone! Tu man papiktinimas, nes mąstai ne apie tai, kas Dievo, o kas žmonių”.
23እርሱ ግን ዘወር ብሎ ጴጥሮስን። ወደ ኋላዬ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን፤ የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና ዕንቅፋት ሆነህብኛል አለው።
24Tuomet Jėzus savo mokiniams pasakė: “Jei kas nori eiti paskui mane, teišsižada pats savęs, teima savo kryžių ir teseka manimi.
24በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አለ። እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ።
25Nes, kas nori išgelbėti savo gyvybę, tas ją praras; o kas praras savo gyvybę dėl manęs, tas ją atras.
25ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታል፤ ስለ እኔ ግን ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ያገኛታል።
26Kokia gi žmogui nauda, jeigu jis laimėtų visą pasaulį, o pakenktų savo sielai? Arba kuo žmogus galėtų išsipirkti savo sielą?
26ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል? ወይስ ሰው ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል?
27Nes Žmogaus Sūnus ateis savo Tėvo šlovėje su savo angelais, ir tuomet Jis atlygins kiekvienam pagal jo darbus.
27የሰው ልጅ ከመላእክቱ ጋር በአባቱ ክብር ይመጣ ዘንድ አለውና፤ ያን ጊዜም ለሁሉ እንደ ሥራው ያስረክበዋል።
28Iš tiesų sakau jums: kai kurie iš čia stovinčių neragaus mirties, kol pamatys Žmogaus Sūnų, ateinantį savo karalystėje”.
28እውነት እላችኋለሁ፥ የሰው ልጅ በመንግሥቱ ሲመጣ እስኪያዩ ድረስ እዚህ ከሚቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ።