1Po šešių dienų Jėzus pasiėmė Petrą, Jokūbą ir jo brolį Joną ir užsivedė juos nuošaliai ant aukšto kalno.
1ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው።
2Ten Jis atsimainė jų akivaizdoje. Jo veidas švietė kaip saulė, o Jo drabužiai tapo balti kaip šviesa.
2በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ።
3Ir štai jiems pasirodė Mozė ir Elijas, kurie kalbėjosi su Juo.
3እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።
4Tada Petras kreipėsi į Jėzų: “Viešpatie, gera mums čia būti! Jei nori, mes pastatysime čia tris palapines: vieną Tau, kitą Mozei, trečią Elijui”.
4ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ።
5Dar jam tebekalbant, štai šviesus debesis apgaubė juos, ir štai balsas iš debesies prabilo: “Šitas yra mano mylimas Sūnus, kuriuo Aš gėriuosi. Jo klausykite!”
5እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።
6Tai išgirdę, mokiniai puolė veidais į žemę ir labai išsigando.
6ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበር።
7Tuomet Jėzus priėjo, palietė juos ir tarė: “Kelkitės, nebijokite!”
7ኢየሱስም ቀርቦ ዳሰሳቸውና። ተነሡ አትፍሩም አላቸው።
8Pakėlę akis, jie nieko daugiau nebematė, tik vieną Jėzų.
8ዓይናቸውንም አቅንተው ሲያዩ ከኢየሱስ ብቻ በቀር ማንንም አላዩም።
9Besileidžiant nuo kalno, Jėzus jiems įsakė: “Niekam nepasakokite apie regėjimą, kol Žmogaus Sūnus prisikels iš numirusių”.
9ከተራራውም በወረዱ ጊዜ ኢየሱስ። የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሣ ድረስ ያያችሁትን ለማንም አትንገሩ ብሎ አዘዛቸው።
10Tada Jo mokiniai Jį paklausė: “Kodėl Rašto žinovai sako, jog pirmiau turįs ateiti Elijas?”
10ደቀ መዛሙርቱም። እንግዲህ ጻፎች። ኤልያስ አስቀድሞ ሊመጣ ይገባዋል ስለ ምን ይላሉ? ብለው ጠየቁት።
11Jėzus atsakė: “Iš tiesų Elijas turi ateiti pirma ir viską atstatyti.
11ኢየሱስም መልሶ። ኤልያስማ አስቀድሞ ይመጣል ሁሉንም ያቀናል፤
12Bet Aš jums sakau, kad Elijas jau atėjo, ir jie jo nepažino, bet padarė su juo, ką norėjo. Taip nuo jų turės kentėti ir Žmogaus Sūnus”.
12ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ኤልያስ ከዚህ በፊት መጣ፤ የወደዱትንም ሁሉ አደረጉበት እንጂ አላወቁትም፤ እንዲሁም ደግሞ የሰው ልጅ ከእነርሱ መከራ ይቀበል ዘንድ አለው አላቸው።
13Tuomet mokiniai suprato, kad Jis kalbėjo jiems apie Joną Krikštytoją.
13በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ስለ መጥምቁ ስለ ዮሐንስ እንደ ነገራቸው አስተዋሉ።
14Jiems atėjus prie minios, priėjo vienas vyras ir puolė prieš Jį ant kelių, sakydamas:
14ወደ ሕዝቡም ሲደርሱ አንድ ሰው ወደ እርሱ ቀረበና ተንበርክኮ። ጌታ ሆይ፥ ልጄን ማርልኝ፥ በጨረቃ እየተነሣበት ክፉኛ ይሣቀያልና፤
15“Viešpatie, pasigailėk mano sūnaus! Jis per miegus vaikščioja ir labai kankinasi: dažnai įpuola į ugnį ir į vandenį.
15ብዙ ጊዜ በእሳት ብዙ ጊዜም በውኃ ይወድቃልና።
16Aš atvedžiau jį pas Tavo mokinius, bet jie nepajėgė išgydyti”.
16ወደ ደቀ መዛሙርትህም አመጣሁት ሊፈውሱትም አቃታቸው አለው።
17Tada Jėzus atsakė: “O netikinti ir iškrypusi karta! Kaip ilgai man reikės su jumis būti? Kaip ilgai jus kęsti? Atveskite jį pas mane”.
17ኢየሱስም መልሶ። የማታምን ጠማማ ትውልድ ሆይ፥ እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ወደዚህ ወደ እኔ አምጡት አለ።
18Jėzus sudraudė demoną, šis išėjo iš berniuko, ir tą pačią akimirką jis pasveiko.
18ኢየሱስም ገሠጸው ጋኔኑም ከእርሱ ወጣ፥ ብላቴናውም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ተፈወሰ።
19Tuomet mokiniai priėjo prie Jėzaus vieni ir klausė: “Dėl ko mes negalėjome jo išvaryti?”
19ከዚህ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ብቻቸውን ወደ ኢየሱስ ቀረቡና። እኛ ልናወጣው ያልቻልን ስለ ምን ነው? አሉት።
20Jėzus jiems atsakė: “Dėl jūsų netikėjimo. Iš tiesų sakau jums: jei turėtumėte tikėjimą kaip garstyčios grūdelį, jūs tartumėte šitam kalnui: ‘Persikelk iš čia į tenai’, ir jis persikeltų. Ir nieko jums nebūtų neįmanomo.
20ኢየሱስም። ስለ እምነታችሁ ማነስ ነው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ። ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም።
21O šita veislė kitaip neišvaroma, kaip tik malda ir pasninku”.
21ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም አላቸው።
22Būdamas su mokiniais Galilėjoje, Jėzus jiems sakė: “Žmogaus Sūnus bus atiduotas į žmonių rankas,
22በገሊላም ሲመላለሱ ኢየሱስ። የሰው ልጅ በሰዎች እጅ አልፎ ይሰጥ ዘንድ አለው፥ ይገድሉትማል፥
23ir jie nužudys Jį, o trečią dieną Jis prisikels”. Tada jie labai nuliūdo.
23በሦስተኛውም ቀን ይነሣል አላቸው። እጅግም አዘኑ።
24Atėjus jiems į Kafarnaumą, prie Petro priėjo didrachmų rinkėjai ir paklausė: “Ar jūsų Mokytojas nemoka didrachmos?”
24ወደ ቅፍርናሆምም በመጡ ጊዜ ግብር የሚቀበሉ ሰዎች ወደ ጴጥሮስ ቀረቡና። መምህራችሁ ሁለቱን ዲናር*ፍ1* አይገብርምን? አሉት።
25Jis atsakė: “Taip!” Kai parėjo į namus, Jėzus pirmas jį prakalbino: “Kaip manai, Simonai? Iš ko žemės karaliai ima muitą ar mokestį: iš savo vaikų ar iš svetimųjų?”
25አዎን ይገብራል አለ። ወደ ቤትም በገባ ጊዜ ኢየሱስ አስቀድሞ። ስምዖን ሆይ፥ ምን ይመስልሃል? የምድር ነገሥታት ቀረጥና ግብር ከማን ይቀበላሉ? ከልጆቻቸውን ወይስ ከእንግዶች? አለው።
26Petras Jam atsakė: “Iš svetimųjų”. Jėzus jam tarė: “Taigi vaikai laisvi.
26ጴጥሮስም። ከእንግዶች ባለው ጊዜ ኢየሱስ። እንኪያስ ልጆቻቸው ነጻ ናቸው።
27Tačiau, kad jų nepapiktintume, nueik prie ežero, užmesk meškerę, paimk pirmą užkibusią žuvį; ją pražiodęs, rasi staterą. Paimk ją ir atiduok jiems už mane ir už save”.
27ነገር ግን እንዳናሰናክላቸው፥ ወደ ባሕር ሂድና መቃጥን ጣል፥ መጀመሪያም የሚወጣውን ዓሣ ውሰድና አፉን ስትከፍት እስታቴር*ፍ2* ታገኛለህ፤ ያን ወስደህ ስለ እኔና ስለ አንተ ስጣቸው አለው።