1Tuo metu prie Jėzaus priėjo mokiniai ir paklausė: “Kas yra didžiausias dangaus karalystėje?”
1በዚያች ሰዓት ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሱስ ቀርበው። በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ የሚበልጥ ማን ይሆን? አሉት።
2Pasišaukęs vaikutį, Jėzus pastatė tarp jų
2ሕፃንም ጠርቶ በመካከላቸው አቆመ
3ir tarė: “Iš tiesų sakau jums: jeigu neatsiversite ir nepasidarysite kaip maži vaikai, niekaip neįeisite į dangaus karalystę.
3እንዲህም አለ። እውነት እላችኋለሁ፥ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።
4Taigi kiekvienas, kas nusižemins kaip šis vaikelis, bus didžiausias dangaus karalystėje”.
4እንግዲህ እንደዚህ ሕፃን ራሱን የሚያዋርድ ሁሉ፥ በመንግሥተ ሰማያት የሚበልጥ እርሱ ነው።
5“Kas priima tokį vaikelį mano vardu, tas mane priima.
5እንደዚህም ያለውን አንድ ሕፃን በስሜ የሚቀበል ሁሉ እኔን ይቀበላል፤
6O kas pastūmėtų į nuodėmę vieną iš šitų mažutėlių, kurie tiki manim, tam būtų geriau, kad girnų akmuo būtų užkabintas jam ant kaklo ir jis būtų paskandintas jūros gelmėje.
6በእኔም ከሚያምኑ ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ሁሉ፥ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር።
7Vargas pasauliui dėl papiktinimų! Papiktinimai neišvengiami, bet vargas tam žmogui, per kurį papiktinimas ateina.
7ወዮ ለዓለም ስለ ማሰናከያ፤ ማሰናከያ ሳይመጣ አይቀርምና፥ ነገር ግን በእርሱ ጠንቅ ማሰናከያ ለሚመጣበት ለዚያ ሰው ወዮለት።
8Jei tavo ranka ar koja traukia tave nusidėti, nukirsk ją ir mesk šalin. Geriau tau sužalotam ar luošam įeiti į gyvenimą, negu su abiem rankom ir kojom būti įmestam į amžiną ugnį.
8እጅህ ወይም እግርህ ብታሰናክልህ፥ ቈርጠህ ከአንተ ጣላት፤ ሁለት እጅ ወይም ሁለት እግር ኖሮህ ወደ ዘላለም እሳት ከምትጣል ይልቅ አንካሳ ወይም ጉንድሽ ሆነህ ወደ ህይወት መግባት ይሻልሀል።
9Ir jeigu tavo akis traukia tave nusidėti, išlupk ją ir mesk šalin. Tau geriau vienakiui įeiti į gyvenimą, negu su abiem akim būti įmestam į pragaro ugnį.
9ዓይንህ ብታሰናክልህ አውጥተህ ከአንተ ጣላት፤ ሁለት ዓይን ኖሮህ ወደ ገሃነመ እሳት ከምትጣል ይልቅ አንዲት ዓይን ኖራህ ወደ ሕይወት መግባት ይሻልሃል።
10Žiūrėkite, kad nepaniekintumėte nė vieno iš šitų mažutėlių, nes, sakau jums, jų angelai danguje visuomet mato mano dangiškojo Tėvo veidą”.
10ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁና።
11“Žmogaus Sūnus atėjo gelbėti, kas buvo pražuvę.
11የሰው ልጅ የጠፋውን ለማዳን መጥቶአልና።
12Kaip jums atrodo: jeigu kas turėtų šimtą avių ir viena nuklystų, argi jis nepaliktų devyniasdešimt devynių ir neitų į kalnus ieškoti nuklydusios?
12ምን ይመስላችኋል? ለአንድ ሰው መቶ በጎች ቢኖሩት ከእነርሱም አንዱ ቢባዝን፥ ዘጠና ዘጠኙን በተራራ ትቶ ሄዶም የባዘነውን አይፈልግምን?
13Ir jei surastųiš tiesų sakau jumsjis džiaugtųsi dėl jos labiau negu dėl devyniasdešimt devynių, kurios nebuvo nuklydusios.
13ቢያገኘውም፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ካልባዘኑቱ ከዘጠና ዘጠኙ ይልቅ በእርሱ ደስ ይለዋል።
14Taip ir jūsų Tėvas, kuris danguje, nenori, kad pražūtų bent vienas iš šitų mažutėlių”.
14እንደዚሁ ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱ እንዲጠፋ በሰማያት ያለው አባታችሁ ፈቃድ አይደለም።
15“Jei tavo brolis tau nusidėtų, eik ir pasakyk jam apie jo kaltę prie keturių akių. Jeigu jis paklausys tavęs, tu laimėjai savo brolį.
15ወንድምህም ቢበድልህ፥ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻችሁን ሆናችሁ ውቀሰው። ቢሰማህ፥ ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው፤
16O jei nepaklausytų, pasiimk su savimi dar vieną ar du, kad ‘dviejų ar trijų liudytojų parodymais būtų patvirtintas kiekvienas žodis’.
16ባይሰማህ ግን፥ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር አፍ ነገር ሁሉ እንዲጸና፥ ዳግመኛ አንድ ወይም ሁለት ከአንተ ጋር ውሰድ፤
17Jeigu jis jų nepaklausytų, pranešk bažnyčiai. O jei neklausys nė bažnyčios, tebūna jis tau kaip pagonis ir muitininkas.
17እነርሱንም ባይሰማ፥ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፥ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ።
18Iš tiesų sakau jums: ką tik jūs surišite žemėje, bus surišta ir danguje, ir ką tik atrišite žemėje, bus atrišta ir danguje”.
18እውነት እላችኋለሁ፥ በምድር የምታስሩት ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል።
19“Ir dar sakau jums: jeigu du iš jūsų susitars žemėje prašyti bet kokio dalyko, jiems mano dangiškasis Tėvas jį suteiks.
19ደግሞ እላችኋለሁ፥ ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል።
20Kur du ar trys susirinkę mano vardu, ten ir Aš esu tarp jų”.
20ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና።
21Tuomet Petras priėjo ir paklausė: “Viešpatie, kiek kartų turiu atleisti savo broliui, kai jis man nusideda? Ar iki septynių kartų?”
21በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ ወደ እርሱ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ወንድሜ ቢበድለኝ ስንት ጊዜ ልተውለት? እስከ ሰባት ጊዜን? አለው።
22Jėzus jam atsakė: “Aš nesakau tau iki septynių kartų, bet iki septyniasdešimt septynių”.
22ኢየሱስ እንዲህ አለው። እስከ ሰባ ጊዜ ሰባት እንጂ እስከ ሰባት ጊዜ አልልህም።
23“Todėl su dangaus karalyste yra panašiai kaip su karaliumi, kuris sumanė atsiskaityti su savo tarnais.
23ስለዚህ መንግሥተ ሰማያት ባሮቹን ሊቈጣጠር የወደደን ንጉሥ ትመስላለች።
24Jam pradėjus apyskaitą, atvedė pas jį vieną, kuris buvo jam skolingas dešimt tūkstančių talentų.
24መቈጣጠርም በጀመረ ጊዜ፥ እልፍ መክሊት ዕዳ ያለበትን አንድ ሰው ወደ እርሱ አመጡ።
25Kadangi šis neturėjo iš ko grąžinti skolą, valdovas įsakė parduoti jį, jo žmoną ir vaikus bei visą jo nuosavybę, kad būtų sumokėta skola.
25የሚከፍለውም ቢያጣ፥ እርሱና ሚስቱ ልጆቹም ያለውም ሁሉ እንዲሸጥና ዕዳው እንዲከፈል ጌታው አዘዘ።
26Tada parpuolęs tarnas jį pagarbino ir tarė: ‘Turėk man kantrybės! Aš viską tau sumokėsiu’.
26ስለዚህ ባሪያው ወድቆ ሰገደለትና። ጌታ ሆይ፥ ታገሠኝ፥ ሁሉንም እከፍልሃለሁ አለው።
27Pasigailėjęs to tarno, valdovas paleido jį ir dovanojo skolą.
27የዚያም ባሪያ ጌታ አዘነለትና ለቀቀው፥ ዕዳውንም ተወለት።
28Vos išėjęs, tas tarnas sutiko vieną savo tarnybos draugą, kuris buvo jam skolingas šimtą denarų, ir nutvėręs smaugė jį, sakydamas: ‘Atiduok skolą!’
28ነገር ግን ያ ባሪያ ወጥቶ ከባልንጀሮቹ ከባሮቹ መቶ ዲናር ዕዳ ያለበትን አንዱን አገኘና። ዕዳህን ክፈለኝ ብሎ ያዘና አነቀው።
29Puolęs ant kelių, draugas maldavo: ‘Turėk man kantrybės! Aš viską sumokėsiu’.
29ስለዚህ ባልንጀራው ባሪያ ወድቆ። ታገሠኝ፥ ሁሉንም እከፍልሃለሁ ብሎ ለመነው።
30Bet tas nesutiko, ėmė ir įmetė jį į kalėjimą, iki atiduos skolą.
30እርሱም አልወደደም፥ ግን ሄዶ ዕዳውን እስኪከፍል ድረስ በወኅኒ አኖረው።
31Matydami, kas nutiko, kiti tarnai labai nuliūdo. Jie nuėjo ir papasakojo valdovui, kas įvyko.
31ባልንጀሮቹ የሆኑ ባሮችም ያደረገውን አይተው እጅግ አዘኑ፥ መጥተውም የሆነውን ሁሉ ለጌታቸው ገለጡ።
32Tada, pasišaukęs jį, valdovas tarė: ‘Nedorasis tarne, visą tavo skolą aš tau dovanojau, nes labai manęs prašei.
32ከዚያ ወዲያ ጌታው ጠርቶ። አንተ ክፉ ባሪያ፥ ስለ ለመንኸኝ ያን ዕዳ ሁሉ ተውሁልህ፤
33Argi neturėjai ir tu pasigailėti savo draugo, kaip aš pasigailėjau tavęs?!’
33እኔ እንደ ማርሁህ ባልንጀራህ የሆነውን ያን ባሪያ ልትምረው ለአንተስ አይገባህምን? አለው።
34Užsirūstinęs valdovas atidavė jį kankintojams, iki jis sumokės visą skolą.
34ጌታውም ተቈጣና ዕዳውን ሁሉ እስኪከፍለው ድረስ ለሚሣቅዩት አሳልፎ ሰጠው።
35Taip ir mano dangiškasis Tėvas pasielgs su jumis, jeigu kiekvienas iš širdies neatleisite savo broliui jo nusižengimų”.
35ከእናንተ እያንዳንዱ ወንድሙን ከልቡ ይቅር ካላለ፥ እንዲሁ ደግሞ የሰማዩ አባቴ ያደርግባችኋል።