Lithuanian

Amharic: New Testament

Philippians

4

1Taigi, mano broliai, mano mylimieji ir išsiilgtieji, mano džiaugsme ir mano vainike,­tvirtai stovėkite Viešpatyje, mylimieji!
1ስለዚህ፥ የምወዳችሁና የምናፍቃችሁ፥ ደስታዬና አክሊሌ የምትሆኑ ወንድሞቼ ሆይ፥ እንዲሁ በጌታ ቁሙ፥ ወዳጆች ሆይ።
2Aš raginu Evodiją ir raginu Sintichę būti vienos minties Viešpatyje.
2በአንድ አሳብ በጌታ እንዲስማሙ ኤዎድያንን እመክራለሁ ሲንጤኪንንም እመክራለሁ።
3Taip pat raginu tave, tikrasis bendradarbi, padėk toms moterims, kurios darbavosi su manimi Evangelijos labui kartu su Klemensu ir kitais mano bendradarbiais, kurių vardai gyvenimo knygoje.
3አንተም ደግሞ በሥራዬ አብረህ የተጠመድህ እውነተኛ ሆይ፥ እንድታግዛቸው እለምንሃለሁ፤ ስሞቻቸው በሕይወት መጽሐፍ ከተጻፉት ከቀሌምንጦስና ደግሞ ከእኔ ጋር አብረው ከሠሩት ከሌሎቹ ጋር በወንጌል ከእኔ ጋር አብረው ተጋድለዋልና።
4Džiaukitės Viešpatyje visuomet! Ir vėl kartoju: džiaukitės!
4ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ።
5Jūsų romumas tebūna žinomas visiems. Viešpats yra arti!
5ገርነታችሁ ለሰው ሁሉ ይታወቅ።
6Niekuo nesirūpinkite, bet visuose reikaluose malda ir prašymu su padėka jūsų troškimai tesidaro žinomi Dievui.
6ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።
7Ir Dievo ramybė, pranokstanti visokį supratimą, saugos jūsų širdis ir mintis Kristuje Jėzuje.
7አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።
8Pagaliau, broliai, mąstykite apie tai, kas tikra, garbinga, teisinga, tyra, mylima, giriama,­apie visa, kas dora ir šlovinga.
8በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ እውነተኛ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ጭምትነት ያለበትን ነገር ሁሉ፥ ጽድቅ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ንጹሕ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ፍቅር ያለበትን ነገር ሁሉ፥ መልካም ወሬ ያለበትን ነገር ሁሉ፥ በጎነት ቢሆን ምስጋናም ቢሆን፥ እነዚህን አስቡ፤
9Darykite, ką tik iš manęs išmokote, ką gavote, ką girdėjote ir matėte manyje, ir ramybės Dievas bus su jumis.
9ከእኔ የተማራችሁትንና የተቀበላችሁትን የሰማችሁትንም ያያችሁትንም እነዚህን አድርጉ፤ የሰላምም አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል።
10Labai nudžiugau Viešpatyje, kad pagaliau vėl pražydo jūsų rūpinimasis manimi. Jūs ir seniau rūpindavotės, bet stigo progų tai parodyti.
10ነገር ግን አሁን ከጊዜ በኋላ ስለ እኔ እንደ ገና ልታስቡ ስለ ጀመራችሁ፥ በጌታ እጅግ ደስ ይለኛል፤ ጊዜ አጣችሁ እንጂ፥ ማሰብስ ታስቡ ነበር።
11Kalbu tai ne todėl, kad stokoju, nes išmokau būti patenkintas savo būkle.
11ይህን ስል ስለ ጉድለት አልልም፤ የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል ማለትን ተምሬአለሁና።
12Esu patyręs ir skurdą, ir perteklių. Visa ko esu ragavęs: buvau sotus ir alkanas, turtingas ir beturtis.
12መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ።
13Aš visa galiu Kristuje, kuris mane stiprina.
13ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።
14Vis dėlto jūs gerai padarėte, dalyvaudami mano varge.
14ሆኖም በመከራዬ ከእኔ ጋር ስለ ተካፈላችሁ መልካም አደረጋችሁ።
15Jūs, filipiečiai, taip pat žinote: kai, pradėjęs skelbti Evangeliją, išvykau iš Makedonijos, jokia bažnyčia neužmezgė su manimi davimo ir gavimo santykių, tik jūs vieni.
15የፊልጵስዩስ ሰዎች ሆይ፥ ወንጌል በመጀመሪያ ሲሰበክ፥ ከመቄዶንያ በወጣሁ ጊዜ፥ ከእናንተ ብቻ በቀር ሌላ ቤተ ክርስቲያን በመስጠትና በመቀበል ስሌት ከእኔ ጋር እንዳልተካፈለች እናንተ ደግሞ ታውቃላችሁ፤
16Jūs mano reikalams pasiuntėte aukų vieną ir kitą kartą į Tesaloniką.
16በተሰሎንቄ እንኳ ሳለሁ፥ አንድ ጊዜና ሁለት ጊዜ ያስፈለገኝን ሰዳችሁልኝ ነበርና።
17Aš netrokštu dovanos, bet trokštu vaisiaus, kuris augtų jūsų sąskaiton.
17በስሌታችሁ የሚበዛውን ፍሬ እንጂ ስጦታውን ፈላጊ አይደለሁም።
18Aš esu visko gavęs ir turiu su pertekliumi. Esu visiškai aprūpintas, per Epafroditą gavęs iš jūsų kvapią dovaną, Dievui priimtiną ir patinkančią auką.
18ነገር ግን ሁሉ አለኝ ይበዛልኝማል፤ የመዓዛ ሽታና የተወደደ መሥዋዕት የሚሆነውን ለእግዚአብሔርም ደስ የሚያሰኘውን ስጦታችሁን ከአፍሮዲጡ ተቀብዬ ተሞልቼአለሁ።
19O mano Dievas patenkins visas jūsų reikmes iš savo šlovės turtų Kristuje Jėzuje.
19አምላኬም እንደ ባለ ጠግነቱ መጠን በክብር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ይሞላባችኋል።
20Mūsų Dievui ir Tėvui šlovė per amžių amžius! Amen.
20ለአምላካችንና ለአባታችንም እስከ ዘላለም ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን።
21Sveikinkite kiekvieną šventąjį Kristuje Jėzuje. Jus sveikina su manimi esantys broliai.
21ለቅዱሳን ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ ሰላምታ አቅርቡ። ከእኔ ጋር ያሉቱ ወንድሞች ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
22Jus sveikina visi šventieji, o ypač iš ciesoriaus namiškių.
22ቅዱሳን ሁሉ ይልቁንም ከቄሣር ቤት የሆኑቱ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
23Viešpaties Jėzaus Kristaus malonė tebūna su jumis visais! Amen.
23የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከመንፈሳችሁ ጋር ይሁን፤ አሜን።