1Esi nepateisinamas, kas bebūtum, žmogau, kuris teisi kitą. Juk teisdamas kitą, pasmerki save, nes ir pats tai darai, už ką teisi.
1ስለዚህ፥ አንተ የምትፈርድ ሰው ሁሉ ሆይ፥ የምታመካኘው የለህም፤ በሌላው በምትፈርድበት ነገር ራስህን ትኰንናለህና፤ አንተው ፈራጁ እነዚያን ታደርጋለህና።
2Mes žinome, kad Dievas teisingai teis tuos, kurie tokius nusikaltimus daro.
2እንደዚህም በሚያደርጉት ላይ የእግዚአብሔር ፍርድ እውነተኛ እንደ ሆነ እናውቃለን።
3Nejaugi manai, žmogau, pats taip darydamas ir teisdamas taip darančius, išvengsiąs Dievo teismo?!
3አንተም እንደዚህ በሚያደርጉ የምትፈርድ ያንም የምታደርግ ሰው ሆይ፥ አንተ ከእግዚአብሔር ፍርድ የምታመልጥ ይመስልሃልን?
4Kaip drįsti niekinti Jo gerumo, pakantumo ir kantrumo turtus? Ar nesupranti, kad Dievo gerumas skatina tave atgailauti?
4ወይስ የእግዚአብሔር ቸርነት ወደ ንስሐ እንዲመራህ ሳታውቅ የቸርነቱንና የመቻሉን የትዕግሥቱንም ባለጠግነት ትንቃለህን?
5Deja, savo užkietėjimu bei neatgailaujančia širdimi tu pats sau kaupi rūstybę Dievo rūstybės ir Jo teisingo teismo apsireiškimo dienai.
5ነገር ግን እንደ ጥንካሬህና ንስሐ እንደማይገባ ልብህ የእግዚአብሔር ቅን ፍርድ በሚገለጥበት በቍጣ ቀን ቍጣን በራስህ ላይ ታከማቻለህ።
6Jis kiekvienam atmokės pagal jo darbus:
6እርሱ ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው ያስረክበዋል፤
7tiems, kurie, ištvermingai darydami gera, ieško šlovės, garbingumo ir nemirtingumo,amžinuoju gyvenimu,
7በበጎ ሥራ በመጽናት ምስጋናንና ክብርን የማይጠፋንም ሕይወት ለሚፈልጉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸዋል፤
8o išpuikėliams, kurie nepaklūsta tiesai, bet yra pasidavę neteisumui,pykčiu ir rūstybe.
8ለዓመፃ በሚታዘዙ እንጂ ለእውነት በማይታዘዙትና በአድመኞች ላይ ግን ቍጣና መቅሠፍት ይሆንባቸዋል።
9Sielvartas ir suspaudimas sielai kiekvieno žmogaus, kuris daro bloga, pirma žydo, paskui graiko.
9ክፉውን በሚያደርግ ሰው ነፍስ ሁሉ መከራና ጭንቀት ይሆንበታል፥ አስቀድሞ በአይሁዳዊ ደግሞም በግሪክ ሰው፤
10Ir šlovė, pagarba bei ramybė kiekvienam, kuris daro gera, pirma žydui, paskui graikui.
10ነገር ግን በጎ ሥራ ለሚያደርጉ ሁሉ ምስጋናና ክብር ሰላምም ይሆንላቸዋል፥ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው።
11Juk Dievas nėra šališkas.
11እግዚአብሔር ለሰው ፊት አያዳላምና።
12Visi, kurie nusidėjo, neturėdami įstatymo, pražus be įstatymo, o visi, kurie nusidėjo, turėdami įstatymą, bus nuteisti pagal įstatymą.
12ያለ ሕግ ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ ያለ ሕግ ደግሞ ይጠፋሉና፤ ሕግም ሳላቸው ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ በሕግ ይፈረድባቸዋል፤
13Ne įstatymo klausytojai teisūs Dievo akyse, bet įstatymo vykdytojai bus išteisinti.
13በእግዚአብሔር ፊት ሕግን የሚያደርጉት ይጸድቃሉ እንጂ ሕግን የሚሰሙ ጻድቃን አይደሉምና።
14Kai jokio įstatymo neturintys pagonys iš prigimties vykdo įstatymo reikalavimus, tada jieneturintys įstatymopatys sau yra įstatymas.
14ሕግ የሌላቸው አሕዛብ ከባሕርያቸው የሕግን ትእዛዝ ሲያደርጉ፥ እነዚያ ሕግ ባይኖራቸው እንኳ ለራሳቸው ሕግ ናቸውና፤
15Jie parodo, kad įstatymo reikalavimai įrašyti jų širdyse, ir tai liudija jų sąžinė bei mintys, kurios tai kaltina, tai teisina viena kitą.
15እነርሱም ሕሊናቸው ሲመሰክርላቸው፥ አሳባቸውም እርስ በርሳቸው ሲካሰስ ወይም ሲያመካኝ በልባቸው የተጻፈውን የሕግ ሥራ ያሳያሉ።
16Aną dieną Dievas per Jėzų Kristų teis žmonių slėpinius, kaip sako mano skelbiama Evangelija.
16ይህም እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ እኔ በወንጌል እንዳስተማርሁ በሰው ዘንድ የተሰወረውን በሚፈርድበት ቀን ይሆናል።
17Štai tu vadiniesi žydas, pasikliauji įstatymu ir giriesi Dievu.
17አንተ ግን አይሁዳዊ ብትባል በሕግም ብትደገፍ በእግዚአብሔርም ብትመካ፥
18Tu žinai Jo valią ir, įstatymo pamokytas, išmanai, kas geriau.
18ፈቃዱንም ብታውቅ ከሕግም ተምረህ የሚሻለውን ፈትነህ ብትወድ፤
19Įsitikinęs, kad esi aklųjų vadovas, šviesa tamsoje esantiems,
19በሕግም የእውቀትና የእውነት መልክ ስላለህ፥ የዕውሮች መሪ፥ በጨለማም ላሉ ብርሃን፥ የሰነፎችም አስተማሪ፥ የሕፃናትም መምህር እንደ ሆንህ በራስህ ብትታመን፤
20neišmanančių mokytojas, kūdikių auklėtojas, turįs įstatyme išreikštą pažinimą ir tiesą.
21እንግዲህ አንተ ሌላውን የምታስተምር ራስህን አታስተምርምን? አትስረቅ ብለህ የምትሰብክ ትሰርቃለህን?
21Tai kodėl tu, mokydamas kitus, nepamokai pats savęs? Kodėl, liepdamas nevogti, pats vagi?
22አታመንዝር የምትል ታመነዝራለህን? ጣዖትን የምትጸየፍ ቤተ መቅደስን ትዘርፋለህን?
22Sakydamas nesvetimauti, pats svetimauji? Bjaurėdamasis stabais, pats apiplėši šventyklas?
23በሕግ የምትመካ ሕግን በመተላለፍ እግዚአብሔርን ታሳፍራለህን?
23Giriesi įstatymu, o paniekini Dievą, laužydamas įstatymą?
24በእናንተ ሰበብ የእግዚአብሔር ስም በአሕዛብ መካከል ይሰደባልና ተብሎ እንደ ተጻፈ።
24Juk parašyta: “Dėl jūsų piktžodžiauja Dievo vardui pagonys”.
25ሕግን ብታደርግ መገረዝስ ይጠቅማል፤ ሕግን ተላላፊ ብትሆን ግን መገረዝህ አለ መገረዝ ሆኖአል።
25Apipjaustymas, tiesa, naudingas, jei vykdai įstatymą. O jeigu esi įstatymo laužytojas, tavo apipjaustymas tampa neapipjaustymu.
26እንግዲህ ያልተገረዘ ሰው የሕግን ሥርዓት ቢጠብቅ አለመገረዙ እንደ መገረዝ ሆኖ አይቈጠርለትምን?
26Taigi, kai neapipjaustytas žmogus laikosi įstatymo reikalavimų, ar jo neapipjaustymas nebus įskaitytas apipjaustymu?
27ከፍጥረቱም ያልተገረዘ ሕግን የሚፈጽም ሰው የሕግ መጽሐፍና መገረዝ ሳለህ ሕግን በምትተላለፈው በአንተ ይፈርድብሃል።
27Ar nuo gimimo neapipjaustytas kūne, bet vykdantis įstatymą nepasmerks tavęs, kuris laužai įstatymą, turėdamas jo raidę ir apipjaustymą?
28በግልጥ አይሁዳዊ የሆነ አይሁዳዊ አይደለምና፥ በግልጥ በሥጋ የሚደረግ መገረዝም መገረዝ አይደለምና፤
28Ne tas yra žydas, kuris išoriškai laikomas žydu, ir ne tas apipjaustymas, kuris išoriškai atliktas kūne.
29ዳሩ ግን በስውር አይሁዳዊ የሆነ አይሁዳዊ ነው፥ መገረዝም በመንፈስ የሚደረግ የልብ መገረዝ ነው እንጂ በመጽሐፍ አይደለም፤ የእርሱ ምስጋና ከእግዚአብሔር ነው እንጂ ከሰው አይደለም።
29Bet tas yra žydas, kuris toks viduje, ir tada yra apipjaustymas, kai širdis apipjaustyta dvasioje, o ne pagal raidę. Tokiam ir šlovė ne iš žmonių, bet iš Dievo.